ኢትዮጵያ የ577.8 ሚሊዮን ዶላር ስደተኞች ዕቅድ ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ የ577.8 ሚሊዮን ዶላር ስደተኞች ዕቅድ ይፋ አደረገች
ኢትዮጵያ የ577.8 ሚሊዮን ዶላር ስደተኞች ዕቅድ ይፋ አደረገች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 12.04.2026
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የ577.8 ሚሊዮን ዶላር ስደተኞች ዕቅድ ይፋ አደረገች

መንግሥት ከ38 አጋሮች በመሆን ያስተዋወቀው የ2026 የስደተኞች ምላሽ ዕቅድ፣ 1.86 ሚሊዮን ስደተኞችንና የአካባቢ ማኅበረሰብን ለመደገፍ ያለመ ነው። ይህም በ2025 መገባደጃ በኢትዮጵያ የሚገኙ 1.12 ሚሊዮን ስደተኞችን ያካትታል።

በሀገሪቱ የሚገኙ ዋና ዋና ስደተኞች፦

ደቡብ ሱዳን፦ 520,896፣
ሶማሊያ፦ 390,603፣
ኤርትራ፦ 183,967 እና
ሱዳን፦ 106,259።

ዕቅዱ ስደተኞች በመደበኛ ሥራዎች እንዲቀጠሩና የንግድ ሥራዎችን እንዲጀምሩ ከሚፈቅደው የጎርጎሮሳውያኑ 2024 "የሥራ መብት መመሪያ" ላይ የተመሠረተ ነው። እስካሁን ከ138,000 በላይ የሚሆኑ ስደተኞች በ‘ፋይዳ’ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት የተመዘገቡ ሲሆን፣ ይህም የባንክ አገልግሎቶችን፣ የሞባይል ሲም ካርዶችን፣ የጤና እና የትምህርት አገልግሎቶችን እንዲያገኙ ያስችላቸዋል።

በጎርጎሮሳዊያኑ 2025 ያጋጠመው የበጀት ቅነሳ የምግብ ዕደላ እንዲቀንስ እንዲሁም ተጨማሪ ድጋፍ ካልተገኘ፣ ቀጣይ ዓመት ከሚያስፈልገው የምግብ አቅርቦት 60 በመቶ ብቻ ይቀርባል መባሉ ስጋት ፈጥሯል ሲል የአገር ውስጥ የግል ጋዜጣ ዘግቧል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0