ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነቱ ተግባራዊ መሆኑን ተከትሎ በሆርሙዝ ወሽመጥ አዲስ የክፍያ ስርዓት ይፋ አድርጋለች

ሰብስክራይብ

ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነቱ ተግባራዊ መሆኑን ተከትሎ በሆርሙዝ ወሽመጥ አዲስ የክፍያ ስርዓት ይፋ አድርጋለች

​ የኢራን የፓርላማ ብሄራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚሽን ሃላፊ እንዳስታወቁት፣ በወሽመጡ በኩል የሚያልፉ ሁሉም መርከቦች በአዲሱ የአስተዳደር እና ቁጥጥር ስርዓት መሠረት ክፍያ እንዲፈጽሙ ይጠበቅባቸዋል።

ኢብራሂም አዚዚ ለሩሲያ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፣ "መንግስት ለሆርሙዝ ወሽመጥ እና ለፋርስ ባህረ ሰላጤ የአስተዳደር እና ቁጥጥር ስርዓት መዘርጋት አለበት። በኢራን ብሄራዊ ጥቅም ላይ ተመስርቶ ለመግባት የሚፈልግ ማንኛውም መርከብ የጉምሩክ ክፍያ መክፈል ይኖርበታል" ብለዋል።

የፓርላማ አባሉ በቅርቡ በኢስላማባድ በተካሄደው የአሜሪካ-ኢራን ንግግር ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ሲሆን፣ ዋሽንግተን ከቴህራን ይልቅ የሰላም ስምምነት እንደሚያስፈልጋት እና ኢራን አሜሪካን እንደማታምን ገልጸዋል።

​ ይህ ማስታወቂያ የወጣው ባለፈው ረቡዕ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ የተኩስ አቁም ስምምነት መደረጉን ተከትሎ ነው። አሜሪካ እና እስራኤል በየካቲት 21 በኢራን ግዛት ላይ ጥቃት የፈጸሙ ሲሆን፣ ኢራንም በእስራኤል እና በአሜሪካ ኢላማዎች ላይ የአጸፋ እርምጃ ወስዳ ነበር።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0