አሜሪካ ወደ ሆርሙዝ ወሽመጥ የሚገቡና የሚወጡ መርከቦችን መግታት ልትጀምር መሆኑን ፕሬዝዳንት ትራምፕ አስታወቁ

የትራምፕ መግለጫ
የትራምፕ መግለጫ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 12.04.2026
ሰብስክራይብ
አሜሪካ ወደ ሆርሙዝ ወሽመጥ የሚገቡና የሚወጡ መርከቦችን መግታት ልትጀምር መሆኑን ፕሬዝዳንት ትራምፕ አስታወቁ


"... ስብሰባው በጥሩ ሁኔታ ተካሂዷል፤ በአብዛኞቹ ነጥቦች ላይ ስምምነት ተደርሷል፣ ነገር ግን ትልቁን ዋጋ የሚሰጠው የኒውክሌር ጉዳይ ግን አልተሳካም" በማለት የአሜሪካ የባህር ኃይል ሆርሙዝን የባህር ውሽመጥ እንደሚቆጣጠር ዶናልድ ትራምፕ በማኅበራዊ ሚዲያቸው ላይ ጽፈዋል።


በሆርሙዝ ለመግባትም ሆነ ለመውጣት የሚሞክሩ ማናቸውም መርከቦች የመገደብ ሂደት ይጀምራል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ የአሜሪካ የባሕር ኃይል በዓለም አቀፍ ውሃዎች ላይ ለኢራን የጉምሩክ ክፍያ የከፈሉ ማናቸውንም መርከቦች እንዲፈልግና እንዲያስቆም መመሪያ ሰጥቻለሁ ብለዋል።


"በእኛ ላይም ሆነ በሰላማዊ መርከቦች ላይ ተኩስ የሚከፍት ማንኛውም ኢራናዊ ወደ ሲኦል ይላካል" ሲሉም ዝተዋል።


በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0