ሩሲያ ለቀጣዩ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊ የምታቀርባቸውን ቁልፍ ጥያቄዎች ይፋ አደረገች

ሩሲያ ለቀጣዩ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊ የምታቀርባቸውን ቁልፍ ጥያቄዎች ይፋ አደረገች
ሩሲያ ለቀጣዩ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊ የምታቀርባቸውን ቁልፍ ጥያቄዎች ይፋ አደረገች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 12.04.2026
ሰብስክራይብ
ሩሲያ ለቀጣዩ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊ የምታቀርባቸውን ቁልፍ ጥያቄዎች ይፋ አደረገች

​ ቀጣዩ የተመድ ዋና ፀሐፊ ሚዛናዊ አቀራረብ ሊኖራቸውና ለተመረጡ ጥቂት ሀገራት ሳይሆን ለሁሉም አባል ሀገራት ጥቅም መሥራት እንደሚኖርባቸው የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለሥልጣን አሳስበዋል፡፡

​በተመድ ባለሥልጣናት መካከል የሚታየው አድልዎ የሚያበቃበት ጊዜ አሁን መሆኑን በሚኒስቴሩ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች መምሪያ ዳይሬክተር ኪሪል ሎግቪኖቭ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

​ ቀጣዩ መሪ የችግሮችን መንስኤ መፍታት እንጂ በአባል ሀገራት ድርጊቶች ላይ ሕጋዊ ግምገማዎችን ከመስጠት መቆጠብ እንዳለባቸው አብራርተዋል። ይህ ደግሞ በዩክሬን ጉዳይ ላይ ብቻ የሚወሰን አለመሆኑን ዲፕሎማቱ አክለው ገልጸዋል።


​"ይህ ተቋም ዳግመኛ የምዕራባውያን አናሳ ቡድኖች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተጨማሪ አካል እንዲሆን አንፈቅድም" ሲሉ ሎግቪኖቭ ተናግረዋል።


በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0