የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን አቅም ለመገንባት ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር አጋርነት እያሰፋሁ ነው - የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር

ሰብስክራይብ
የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን አቅም ለመገንባት ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር አጋርነት እያሰፋሁ ነው - የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር

​ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ጋር አጋርነት መመሥረቱን የገለጹት ሚኒስትር ዲኤታ በርኦ ሐሰን፣ በእነዚህ ተቋማት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ጥገና እና አሠራር ለማጠናከር የሚያስችሉ ምርምሮች እየተካሄዱ መሆኑንም ጠቁመዋል።

አክለውም፣ በተለይም በባትሪ አያያዝ እና አገልግሎት የጨረሱ ባትሪዎችን ዳግም ጥቅም ላይ በማዋል ረገድ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን ለአገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል።

ይህ ተነሳሽነት ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ከፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ጋር በትብብር ይተገበራል።

ቪዲዮው በአዲስ አበባ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴን ያሳያል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0