- Sputnik አፍሪካ, 1920
Turning Africa Forward
በአህጉሪቱ ስልታዊ መነቃቃት ላይ ግልጽ እይታን የሚሰጥ በስፑትኒክ አፍሪካ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ፕሮግራም ። ከዜናዎች ባሻገር፣ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካ ውስጥ ያላትን እየተለወጠ የመጣ ሚና በጥልቀት ይተነትናል፤ የወደፊቱን የዓለም ሥርዓት በመቅረጽ ረገድ ያለውን አቅጣጫ በሰፊው ይዳስሳል።

የስፔስ ቴክኖሎጂ፡- የአፍሪካ ስትራቴጂካዊና መጻኢ እድል

የስፔስ ቴክኖሎጂ፡ የአፍሪካ ስትራቴጂካዊና መጻኢ እድል
ሰብስክራይብ
"የስፔስ ቴክኖሎጂ እዚሁ ቤታችን ነው፣ አጠገባችን ነው ያለው። ግብርናችን ጋር አለ። የምንሳፈርበት ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ አለ። የስፔስ ቴክኖሎጂ ያልገባበት ቦታ የለም።... ያለ ስፔስ ቴክኖሎጂ ወደፊት መሄድ አንችልም ማለት ነው።... ስለዚህ የስፔስ ቴክኖሎጂ ሁሉ ነገራችን እየሆነ መጥቷል።" ሲሉ የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ እና ጂዮስፓሺያል ኢንስቲቱት ም/ል ዋና ዳይሬክተር ይሽሩን አለማየሁ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታቸን አፍሪካ በህዋ ሳይንስ ያላትን አዲስ ምዕራፍ እና በምስራቅ አፍሪካ እየተገነቡ ያሉ ወታደራዊ ትብብሮችን በጥልቀት እንመረምራለን። ክፍል አንድ፦ ዩሪ ጋጋሪን ወደ ህዋ ከመጠቀ ከ65 ዓመታት በኋላ፣ አፍሪካ በሳተላይት ቴክኖሎጂ ያላት ተሳትፎ የት ደረሰ? የኢትዮጵያ ETRSS 2 ሳተላይት ምጥቀትስ ለአህጉራዊ አጋርነት ምን ትርጉም አለው? በጉዳዩ ላይ ይሽሩን አለማየሁ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ እና ጂዮስፓሺያል ኢንስቲቱት ም/ል ዋና ዳይሬክተር ሰፊ ትንታኔ ይሰጡናል። በክፍል ሁለት፦ የታሪክ ድርና ማግ! ኢትዮጵያና ታንዛኒያ ከ1950ዎቹ የጀመረውን ወታደራዊ ትስስር ዛሬ ላይ እንዴት እያደሱት ነው? የኢትዮጵያ አየር ኃይል የበላይነት ለቀጠናው ደህንነትና ለጸረ-ሽብር ትግሉ ያለው ፋይዳ ምንድን ነው? የሰላምና ጸጥታ እና የአካባቢ ጉዳዮች ተንታኙ አቶ ዮሴፍ ወልደኪዳን ማብራሪያ ይዘው ቀርበዋል።

ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ይከታተሉ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0