ኢትዮጵያ እስከ ጎርጎሮሳውያኑ 2030 ድረስ 16 አዳዲስ መርከቦችን የማሰማራት እቅዷን ይፋ አደረገች
20:04 10.04.2026 (የተሻሻለ: 20:14 10.04.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ እስከ ጎርጎሮሳውያኑ 2030 ድረስ 16 አዳዲስ መርከቦችን የማሰማራት እቅዷን ይፋ አደረገች
ይህ የማስፋፊያ ዕቅድ ዓመታዊ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ወደ 1.7 ቢሊዮን ዶላር ለማሳደግ እና እስከ 2030 ድረስ ገቢን ወደ 295 ቢሊዮን ብር የማድረስ ስትራቴጂ አካል መሆኑን የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አብዱልበር ሸምሱ ለአገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡
በመጪዎቹ አምስት ዓመታት የአገልግሎት ሞዴሉን ከሁለተኛ ወገን ሎጂስቲክስ (2PL)፣ ሙሉ በሙሉ የሦስተኛ ወገን ሎጂስቲክስ (3PL) አቅራቢነት ማሳደግ የድርጅቱ ስትራቴጂካዊ ለውጥ አካልነት ነው፡፡ ይህም ይበልጥ የተቀናጁ እና እሴት የሚጨምሩ አገልግሎቶችን ለመስጠት እንደሚያስችል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገልጸዋል።
ኩባንያው የራሱን 10 መርከቦች፣ ወደ 60 የሚጠጉ የኪራይ መርከቦች እና ተጨማሪ የቦታ ስምምነቶችን በማስተዳደር በዓለም ዙሪያ ከ370 በላይ ወደቦችን ያዳርሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X