የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሁለት ምዕራፍ የሚተገበር የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች ግንባታን ይፋ አደረገ

ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሁለት ምዕራፍ የሚተገበር የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች ግንባታን ይፋ አደረገ

10 ሚሊዮን ዶላር የተመደበለት የመጀመሪያው ምዕራፍ፣ በአዲስ አበባ እና በአቅራቢያዋ ባሉ ከተሞች የ40 ጣቢያዎች ግንባታ የያዘ ሲሆን 3 ጣቢያዎች ከዚህ በፊት ተመርቀዋል።

እያንዳንዱ ጣቢያ በአንድ ጊዜ 24 ተሽከርካሪዎችን የማስተናገድ አቅም አለው። የአገልግሎት ክፍያው በኪሎ ዋት ሠዓት ከ14 እስከ 18 የኢትዮጵያ ብር ሆኖ ተቆርጧል።

የሁለተኛ ምዕራፍ ግንባታው ወደ ክልል ከተሞች (ቢሾፍቱ፣ ሞጆ፣ አዳማ፣ ሻሸመኔ እና ሐዋሳ) እንደሚስፋፋ የአገልግሎቱን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጠቅሶ የውጭ ሚዲያ ዘግቧል።

አገልግሎቱ በአዲስ አበባ ሠዓሊተ ምህረት አካባቢ አስገንብቶ ሥራ ያስጀመረው ጣቢያ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0