'በናይጄሪያ ውስጥ፣ በናይጄሪያውያን መሐንዲሶች፣ በራሳችን መሬት ላይ ሳተላይት መገንባት እንፈልጋለን' - የህዋ ኤጀንሲ ዋና ስራ አስፈጻሚ

ሰብስክራይብ

'በናይጄሪያ ውስጥ፣ በናይጄሪያውያን መሐንዲሶች፣ በራሳችን መሬት ላይ ሳተላይት መገንባት እንፈልጋለን' - የህዋ ኤጀንሲ ዋና ስራ አስፈጻሚ

​የዩሪ ጋጋሪን ታሪካዊ በረራ የናይጄሪያን የህዋ ምኞት ማነሳሳቱን ቀጥሏል ሲሉ ሀገሪቱ ከሩሲያ ጋር ያላትን አጋርነት በማጠናከር፤ የዓለም "ኮስሞናውትስ" (የጠፈርተኞች) ቀንን እያከበረች ነው ሲሉ የብሔራዊ የህዋ ምርምር እና ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ማቲው አዴፖጁ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ናይጄሪያ፣ "በኤጀንሲው ውስጥ ከ5,000 በላይ ሰራተኞች ያሏት ሲሆን፣ ... እኔን ጨምሮ 300 ያህል ፒ.ኤች.ዲ. የያዙ ባለሙያዎች አለን" ሲሉ ገልጸዋል።

የሩሲያ ልዩ ባለሙያዎች በቅርቡ በናይጄሪያና መሐንዲሶች የቅኝት ማዕከል ውስጥ ስልጠናዎችን የሰጡ ሲሆን፣ ተጨማሪ ልውውጦችም ታቅደዋል ሲሉ ዳይሬክተሩ አክለዋል።

​"ከሩሲያውያን የምናገኘው ጥቅም በጣም ብዙ ነው። ... እየደገፉን ነው፣ ነገር ግን ያንን ግንኙነት ከአስትሮኖሚ እና አስትሮፊዚክስ ባለፈ የበለጠ ማጠናከር አለብን። ወደ ሳተላይት ልማት፣ ወደ ሮኬት ልማት እና ወደመሳሰሉት ዘርፎች ማሸጋገር እንፈልጋለን።"

የብሄራዊ ተቋሙን ተልዕኮ "በሳተላይት ልማት፣ በሮኬት ልማት፣ በትግበራዎች፣ በዳታ ሳይንስ እና በሌሎችም ዘርፎች የሀገር በቀል አቅምን ማሳደግ" ነው።



ስለ ናይጄሪያ የህዋ ተቋም እድገቶች የበለጠ ለማወቅ ቪዲዮውን ይመልከቱ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0