በአውሮፓ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ "አሳሳቢ አዝማሚያ ነው" - ዛካሮቫ
19:55 08.04.2026 (የተሻሻለ: 20:04 08.04.2026)
ሰብስክራይብ
በአውሮፓ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ "አሳሳቢ አዝማሚያ ነው" - ዛካሮቫ
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ የሰጧቸው ሌሎች ተጨማሪ መግለጫዎች፦
◻ በአውሮፓ ሀገራት ዘንድ እየታየ ያለው የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ድጋፍ ንቅናቄ፤ ዓለም አቀፉን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ የቁጥጥር ሥርዓት እያዳከመና እየሸረሸረ ይገኛል፡፡
◻ ሞስኮ በኢራን እና በአሜሪካ መካከል የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት በደስታ ትቀበላለች፡፡ ግጭቱ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈታ ገና ከጅምሩ ስትሟገት ቆያታለች፡፡
◻ እንደ ኢራን ግጭት ያሉ ሰው ሠራሽ ቀውሶች ዳግመኛ እንዳይከሰቱ ለመከላከል አስተማማኝ ዋስትናዎች ያስፈልጋሉ፡፡
◻ በባህሬን ቀርቦ በሞስኮ እና በቤጂንግ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት ውድቅ የተደረገው የጸጥታው ምክር ቤት የውሳኔ ሃሳብ ቢጸድቅ ኖሮ ለዓለም አቀፍ ሕግ አደገኛ ምሳሌ ሊፈጥር ይችል ነበር፡፡
◻ ዩክሬን ለዓለም አቀፍ የመረጃ ደህንነት ዘላቂ ስጋት መሆኗን የጠቀሱት ቃል አቀባይዋ፤ ሀገሪቱ ለሳይበር ወንጀለኞች መሸሸጊያ ሆናለች ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X