በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት መደረጉን ተከትሎ በአውሮፓ የጋዝ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ቀነሰ

የጋዝ ዋጋ
የጋዝ ዋጋ  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.04.2026
ሰብስክራይብ
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት መደረጉን ተከትሎ በአውሮፓ የጋዝ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ቀነሰ

በለንደን የንግድ መለዋወጫ ተቋም መረጃ መሠረት፤ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት መደረጉን የሚጠቁሙ ዘገባዎች መውጣታቸውን ተከትሎ በአውሮፓ የተፈጥሮ ጋዝ ዋጋ በ18.5 በመቶ ቀንሷል።

በኔዘርላንድስ የሚገኘው ትልቁ የአውሮፓ የጋዝ ማከፋፈያ ማዕከል የግንቦት ወር ውል የ18.5 በመቶ ቅናሽ በማሳየት በ1,000 ኩቢክ ሜትር 518.6 ዶላር ተከፍቷል።

በኋላ ዋጋው መጠነኛ ጭማሪ በማሳየት 529.3 ዶላር (-16.8 በመቶ) ደርሷል።

ባለፈው የንግድ ቀን የነበረው የመዝጊያ ዋጋ 597.6 ዶላር ነበር።

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ለሁለት ሳምንታት ለማቆም መስማማታቸውንና የተኩስ አቁም ስምምነቱ በሁለቱም ወገኖች በኩል ተፈጻሚ እንደሚሆን ቀደም ብለው አረጋግጠዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0