ጋና ከ20 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የዳማንግ የወርቅ ማዕድን ቁፋሮ ፈቃድ ለሀገር በቀል ኩባንያ ሰጠች

ጋና
ጋና  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.04.2026
ሰብስክራይብ
ጋና ከ20 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የዳማንግ የወርቅ ማዕድን ቁፋሮ ፈቃድ ለሀገር በቀል ኩባንያ ሰጠች

የጋና የማዕድን ኮሚሽን ጨረታው "ኢንጂነርስ ኤንድ ፕላነርስ" ለተሰኘው የሀገር ውስጥ ኩባንያ እንዲሰጥ ምክረ ሃሳብ ማቅረቡን የመሬትና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስትሩ አማኑኤል አርማህ-ኮፊ ቡአህ አስታውቀዋል።


ሚኒስትሩ አክለውም "የጨረታ ሰነዱ ኩባንያው ከዳማንግ ማዕድን ቁፋሮ ሥራ፣ ከመሠረተ ልማት እና ከሥነ-ምድር ጋር የተያያዙ ተገቢ ልምዶችና እውቀቶች አሉት" ብለዋል።


በ505 ሚሊዮን ዶላር መንግሥት ተጫራቾች እንዲያሟሉ ያስቀመጠውን አነስተኛ የገንዘብ አቅም መስፈርት ማሟላቱን ሚኒስትሩ አፅንዖት ሰጥተው ገልፀዋል።


"ባጭሩ ኩባንያው ባቀረበው እጅግ አዋጭ የጨረታ ሰነድ የዳማንግ ማዕድንን የማንቀሳቀስ ከፍተኛ ብቃት እንዳለው አሳይቷል" ሲሉ ተናግረዋል።


የወርቅ ማዕድን ማውጫው ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በደቡብ አፍሪካው "ጎልድ ፊልድስ" ኩባንያ ስር እንደነበር የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0