እንግሊዝ የባሪያ ንግድ ካሳ ለሚጠይቁ ሀገራት ዜጎች ቪዛ መከልከል አለባት - የሪፎርም ዩኬ ፓርቲ

ሰብስክራይብ

እንግሊዝ የባሪያ ንግድ ካሳ ለሚጠይቁ ሀገራት ዜጎች ቪዛ መከልከል አለባት - የሪፎርም ዩኬ ፓርቲ

ለባሪያ ንግድ ካሳ የሚጠይቁ ሀገራት (አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት) ዜጎች ወደ እንግሊዝ እንዳይገቡ መከልከል አለባቸው ሲሉ የፓርቲው ሊቀመንበር ዚያ ዩሱፍ ተናግረዋል።

"ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥራቸው እየጨመረ የመጣ ሀገራት ከብሪታንያ ካሳ እየጠየቁ ይገኛሉ። እነዚህ ሀገራት ብሪታንያ ባርነትን በሕግ ለማገድ እና ክልከላውን ለማስፈጸም የመጀመሪያዋ ትልቅ ኃይል በመሆን የከፈለችውን ከፍተኛ መስዋዕትነት ይዘነጋሉ" ሲሉ ለብሪታንያ መገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።

አስተያየቱ በቅርቡ በጋና መሪነት የአትላንቲክ ባሪያ ንግድን "በሰው ልጅ ላይ የተፈጸመ ከባድ ወንጀል" ሲል በመፈረጅ የካሳ ክፍያ ጥሪ ያቀረበው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ በተላለፈ ማግስት የመጣ ነው። እንግሊዝ እና የአውሮፓ ኅብረት አባል ሀገራት ድምፀ ተአቅቦ ሲያደርጉ፤ አሜሪካ፣ እስራኤል እና አርጀንቲና ደግሞ ተቃውሟቸውን ገልፀዋል።

በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0