ለኢትዮጵያ ጭነቶች ቅድሚያ እንሰጣለን - ጂቡቲ

ኢትዮጵያ፣ ጂቡቲ
ኢትዮጵያ፣ ጂቡቲ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 07.04.2026
ሰብስክራይብ
ለኢትዮጵያ ጭነቶች ቅድሚያ እንሰጣለን - ጂቡቲ

በፋርስ ባሕረ ሰላጤ በተከሰተው ግጭት ምክንያት ወደ ጂቡቲ ወደቦች የሚመጡ መርከቦች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ቢጨምርም፤ የኢትዮጵያ ጭነቶች ቅድሚያ እንደሚሰጣቸው የጂቡቲ የወደቦችና ነፃ ቀጣና ባለሥልጣን አስታውቋል።


“ይህንን ችግር እኛ አልፈጠርነውም። ስለዚህ ኢትዮጵያን መዳረሻቸው ላደርጉ የኢትዮጵያ ጭነቶች ቅድሚያ እንሰጣለን” ሲሉ የባለሥልጣኑ ሰብሳቢ አቡበከር ዑመር ሃዲ ነግረውኛል ሲል የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡


ባለሥልጣኑ አክለውም ጂቡቲ ስድስት ጥልቅ የባሕር ወደቦችና በቂ መሠረተ ልማት ያሏት በመሆኑ በወደብ መጨናነቅ ምክንያት የሚፈጠር ጫናን የመቋቋም አቅም እንዳላት አብራርተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0