ብዙ አፍሪካውያን እውነተኛ መንፈሳዊነትን ፍለጋ ወደ ሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ፊታቸውን እያዞሩ ነው - ቄስ

ሰብስክራይብ

ብዙ አፍሪካውያን እውነተኛ መንፈሳዊነትን ፍለጋ ወደ ሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ፊታቸውን እያዞሩ ነው - ቄስ

በሚድራንድ ደቡብ አፍሪካ የቅዱስ ሰርጊየስ ኦፍ ራዶኔዝ ቤተ-ክርስቲያን አስተዳዳሪ ሊቀ ካህናት ዳኒል ሉጎቮይ፤ በተለያዩ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ጥልቅ በሆነ የግል ውሳኔ እና ግንኙነት ወደ እምነቱ እየመጡ እንደሚገኙ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

"ብዙውን ጊዜ አንድ ሰው ወደ ኦርቶዶክስ እምነት የሚመጣው ነገሩ አዲስ ወይም እንግዳ ስለሆነበት ሳይሆን በሆነ ወቅት የተሟላ መንፈሳዊ ሕይወትን መፈለግ ስለሚጀምር ነው" ሲሉ አክለዋል።

በሩሲያ ባሕል፣ በሥዕለ አድኅኖ ወይም በቤተ-ክርስቲያን ዝማሬ የሚጀመረው ፍላጎት ቀስ በቀስ ወደ ቤተ-ክርስቲያኗ እንደሚመራም ሊቀ ካህናት ዳኒል ሉጎቮይ ገልጸዋል።

ለሌሎች ደግሞ መንገዱ የሚጀምረው በግል ቀውስ ወይም ጥልቅ የሆነ የክርስትና ባሕልን ከመፈለግ ቢሆንም፤ ሂደቱ ሁልጊዜም ከባድ ልባዊ ግፊት ይጠይቃል።

በቪዲዮው አምስት የሞሪሸስ ነዋሪዎች በሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ የጥምቀት ሥርዓት ሲፈጽሙ ይታያል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0