ዓለም አቀፉ የቶማስ ሳንካራ መታሰቢያ ኮሚቴ ስለአፍሪካውያን ነፃነት እያስተዋወቀ መሆኑን የኮሚቴው አባል ገለፁ

ሰብስክራይብ

ዓለም አቀፉ የቶማስ ሳንካራ መታሰቢያ ኮሚቴ ስለአፍሪካውያን ነፃነት እያስተዋወቀ መሆኑን የኮሚቴው አባል ገለፁ

ኮሚቴው የአኅጉሪቱን ሉዓላዊነት እና እውነተኛ ነፃነት ለማረጋገጥ የሳንካራን እሴቶች የማስፋፋት ዓላማ እንዳለው ሱሌይማን ዜርቦ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

"ሳንካራ ለአፍሪካ እና ለአኅጉሪቱ እድገት ምን ይመኝ እንደነበር፣ እርሱን ለማያውቁ ወጣቶች ማስረዳት መቻል አለብን። እነዚህን እሴቶች ለወጣቶቻችን ካስተማርናቸው፣ ወደፊት ጥሩ መሪዎች ይሆናሉ" ሲሉ ገልጸዋል።

ቶማስ ሳንካራ ከታች የተጠቀሱትን ጨምሮ ለአፍሪካ አሁን ይበልጥ በጣም አስፈላጊ የሆኑ እሴቶችን ሲያቀነቅን እንደነበርም አብራርተዋል፦

🟠 የሴቶችን መብት ማስከበር (ተንቀሳቃሽ ምስሉን ይመልከቱ)፣

🟠 በረሃማነትን መዋጋት፣

🟠 የአካባቢ ጥበቃ፣

🟠 መልካም አስተዳደር።

ℹ ዓለም አቀፉ የቶማስ ሳንካራ መታሰቢያ ኮሚቴ እ.ኤ.አ በ2016 የሳንካራ የቅርብ ጓደኛ በነበሩት ጄሪ ራውሊንግስ የተመሠረተ ሲሆን የሳንካራን አሻራ እና እሴቶች ማነቃቃት እንዲሁም በሳንካራ የላቀ አስተሳሰብ ዙሪያ ወጣቶችን የማስተማር ዓላማ አለው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0