በአፍሪካ የሚገኙ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ሰበካዎች ቁጥር ከ300 በላይ ደረሰ

ሰብስክራይብ

በአፍሪካ የሚገኙ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ሰበካዎች ቁጥር ከ300 በላይ ደረሰ

“በአፍሪካ የቤተ-ክርስቲያኒቱ ዋና ተግባር ሰዎች በእውነት በቤተ-ክርስቲያን ውስጥ መኖር እንዲጀምሩ መርዳት ነው፡፡ ይህም ሐይማኖትን እንዲማሩ፣ በጸሎትና በሥርዓተ አምልኮ እንዲሳተፉ፣ በመንፈሳዊ ሁኔታ እንዲያድጉ እና የኅብረተሰቡ አካል እንደሆኑ እንዲሰማቸው ማድረግ ነው” ሲሉ የቅዱስ ሰርጊየስ ኦፍ ራዶኔዥ ቤተ-ክርስቲያን አስተዳዳሪ ሊቀ ካህናት ዳኒል ሉጎቮይ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

ደብሮቹ ከዚህ ቀደም ትኩረታቸው የሩሲያ ቋንቋ ተናጋሪ ዳያስፖራዎችን ማገልገል ብቻ የነበረ ቢሆንም፤ ዛሬ ግን በአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ በልማት፣ በሐይማኖት ትምህርት፣ በካህናት ሥልጠና እና በሥርዓታዊ የሚሲዮናዊ ሥራ ተሳትፎ እያደረጉ እንደሆነ ገልጸዋል።

በሌላ አነጋገር “ከተበታተኑ አጥቢያዎች ወደ ተቀናጀ እና ዘላቂ የቤተ-ክርስቲያን እንቅስቃሴ ሽግግር እየተደረገ መሆኑን እያየን ነው” ሲሉ ገልፀዋል።

በቅርቡ በአፍሪካ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ሀገረ ስብከት ይፋ የተደረገው ተንቀሳቃሽ ምስል አንድ ናይጄሪያዊ ሲጠመቅ ያሳያል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0