ኢራን በቡሸር የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የተፈጸመው ድብደባ የጦር ወንጀል ማሳያ መሆኑን ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ገለፀች

ኢራን
ኢራን - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.04.2026
ሰብስክራይብ
ኢራን በቡሸር የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የተፈጸመው ድብደባ የጦር ወንጀል ማሳያ መሆኑን ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ገለፀች

ቴህራን ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ በላከችው አቤቱታ፤ በቡሸር የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ አሜሪካና እስራኤል የፈጸሙትን ድብደባ እንዲያወግዙ መጠየቋን የኢራን የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

የኢራን የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ኃላፊ መሐመድ ኤስላሚ ለግሮሲ በሰጡት ማብራሪያ "በቡሸር ጣቢያ የመጀመሪያው ክፍል አካባቢ የተፈጸመው የቅርብ ጊዜ ጥቃት ዓለም አቀፍ ደንቦችን የጣሰ ነው" ብለዋል።

ኃላፊው ኢራን ራሷን ለመከላከል አስፈላጊውን እርምጃ እንደምትወስድ መግለጻቸውንም ድርጅቱ አመልክቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0