በግብፅ በልብ ጡንቻ ውስጥ አምስት ሴንቲ ሜትር የሚረዝም ሚስማር የገባበት ህፃን በሕክምና ተረፈ

ግብፅ
ግብፅ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.04.2026
ሰብስክራይብ
በግብፅ በልብ ጡንቻ ውስጥ አምስት ሴንቲ ሜትር የሚረዝም ሚስማር የገባበት ህፃን በሕክምና ተረፈ

አንድ የ11 ዓመት ታዳጊ በሚስማር መምቻ መሣሪያ ሲጫወት በደረሰበት አደጋ ሚስማሩ ደረቱን ሰንጥቆ በቀጥታ የልብ ጡንቻው ውስጥ በመግባቱ፤ በከባድ ሁኔታ ላይ ሆኖ በካይሮ ወደሚገኘው የቃስር አል አይኒ ሆስፒታል መድረሱን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

‍ ከሆስፒታሉ የልብና የደረት ቀዶ ጥገና ክፍል የተውጣጣ ልዩ የሕክምና ቡድን ሚስማሩን በተሳካ ሁኔታ በማውጣትና ደም መፍሰሱን በማቆም የታዳጊውን ሕይወት እንደታደገ ዘገባው አመልክቷል።

ከሁለት ቀናት በኋላም ህፃኑ ከሆስፒታል መውጣቱ ተገልጿል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0