አሜሪካ “አሮጌ” ኤ-10 የጦር አውሮፕላኖችን በኢራን አሰማራች

ኤ-10 የጦር አውሮፕላኖች
ኤ-10 የጦር አውሮፕላኖች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.04.2026
ሰብስክራይብ
አሜሪካ “አሮጌ” ኤ-10 የጦር አውሮፕላኖችን በኢራን አሰማራች

የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር (ፔንታገን) ለከባድ ዘመናዊ ጦርነቶች ብቁ እንዳልሆኑ ያመናቸውን ኤ-10 ታንደርቦልት 2 ተዋጊ ጄቶችን ኢራን ላይ እየተጠቀመ መሆኑን የአሜሪካ የበጀት ሰነዶችና ሕጎች ያሳያሉ።

አየር ኃይሉ 423 ሚሊዮን ዶላር ለመቆጠብ የቀሩትን 162 የኤ-10 አውሮፕላኖች በሙሉ ከአገልግሎት ለማስወጣት አቅዶ ነበር። የ2025 የመከላከያ ሕግ ግን የአውሮፕላኖቹን ቁጥር የመቀነስ ዕቅድ ለጊዜው በማቆም እስከ 2029 ድረስ ሙሉ በሙሉ ከሥራ እንደሚወጡ አረጋግጧል።

ሆኖም አውሮፕላኖቹ በአሁኑ ወቅት በመካከለኛው ምስራቅ ተሰማርተዋል። ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ እንደዘገበው፤ አሜሪካ ለ ‘ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ’ ዘመቻ የኤ-10 ጦር አውሮፕላኖች ስምሪቷን በእጥፍ በመጨመር ወደ 30 አሳድጋለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0