የናይጄሪያ ወታደሮች ቤተ-ክርስቲያን ላይ የተቃጣን ጥቃት አከሸፉ

ናይጄሪያ
ናይጄሪያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.04.2026
ሰብስክራይብ
የናይጄሪያ ወታደሮች ቤተ-ክርስቲያን ላይ የተቃጣን ጥቃት አከሸፉ

የናይጄሪያ ወታደሮች በካዱና ግዛት በሚገኝ አንድ ቤተ-ክርስቲያን የትንሳኤ በዓል ሥነ-ሥርዓት ላይ የነበሩ ምዕመናን በአሸባሪዎች እየታፈኑ ነው የሚል አስቸኳይ ጥሪ እንደደረሳቸው ፈጣን ምላሽ መስጠታቸውን ጦር ሠራዊቱ አስታውቋል።

ወታደሮቹ የአካባቢው ነዋሪዎች በሰጧቸው መረጃ በመታገዝ ወዲያውኑ አጥቂዎቹን በማሳደድ አሸባሪዎቹ ታጋቾቹን ጥለው እንዲሸሹ ማድረገቻው ተገልጿል።

በአሸባሪዎቹ የተገደሉ አምስት የጥቃቱ ሰለባዎች አስከሬን በቦታው የተገኘ ሲሆን በሸሹት አጥቂዎች በኩልም ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው የሚያሳዩ የደም ዱካዎች መታየታቸውን መግለጫው ጠቁሟል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0