ላቭሮቭ እና አራግቺ በኢራን የሲቪል እና የኢነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች እንዲቆሙ አሳሰቡ - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

ላቭሮቭ እና አራግቺ በኢራን የሲቪል እና የኢነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ
ላቭሮቭ እና አራግቺ በኢራን የሲቪል እና የኢነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 05.04.2026
ሰብስክራይብ
ላቭሮቭ እና አራግቺ በኢራን የሲቪል እና የኢነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች እንዲቆሙ አሳሰቡ - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

​የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እና የኢራኑ አቻቸው አባስ አራግቺ በዛሬው ዕለት የስልክ ውይይት አድርገዋል።

​የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ የቡሸር የኒውክሌር ኃይል ማመንጫን ጨምሮ በኢራን ቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች እንዲቆሙ አሳስበዋል። ይህም ለመላው ቀጣና የራዲዮአክቲቭ አደጋ ስጋት ሊፈጥር እንደሚችል ገልጸዋል።

​በተጨማሪም፣ ሚኒስትሮቹ ሰላማዊ ጥረቶችን ሊያደናቅፉ የሚችሉ፣ እንዲሁም የዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ፍለጋን እና ውጥረትን የማርገብ እድሎችን የሚያጠፉ ድርጊቶች እንዲወገዱ ጥሪ አቅርበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0