ጋና በአፍሪካ ባለሙያዎች ላይ የሚደረገውን አድልዎ በመጥቀስ በእንግሊዝ በሚካሄደው የኢነርጂ ጉባኤ ላለመካፈል ወስናለች - የኢነርጂ ምክር ቤት
16:40 05.04.2026 (የተሻሻለ: 17:16 05.04.2026)

ሰብስክራይብ
ጋና በአፍሪካ ባለሙያዎች ላይ የሚደረገውን አድልዎ በመጥቀስ በእንግሊዝ በሚካሄደው የኢነርጂ ጉባኤ ላለመካፈል ወስናለች - የኢነርጂ ምክር ቤት
የአኅጉሪቱን የኢነርጂ የወደፊት ሁኔታ ይወክላሉ በሚባሉ ሁነቶች ላይ የአፍሪካ ባለሙያዎች መገለላቸውን በመቃወም፣ በግንቦት ወር አጋማሽ በለንደን በሚካሄደው የአፍሪካ ኢነርጂ ጉባኤ ላይ ላለመሳተፍ መወሰኗን የጋና የኢነርጂ ምክር ቤት አስታዉቋል።
ምክር ቤቱ አዘጋጆቹ መለካት የሚችል የአካታችነት ማረጋገጫ እስኪያሳዩ ድረስ የአካባቢው ባለስልጣናት ተሳትፎአቸውን እንዲያጤኑት ጠይቋል። ይህም ሞዛምቢክን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ካስተላለፉት ተመሳሳይ ውሳኔ በመቀጠል የመጣ ነው።
“ጋና በአፍሪካ የኢነርጂ ታሪክ ውስጥ ተመልካች አይደለችም። ... አፍሪካ ለተሳትፎ ብቻ እንደ ገበያ የምትቆጠርበት እንዲሁም አፍሪካውያን በተግባራዊ አፈጻጸም ላይ እንደ አማራጭ ተሳታፊ የሚታዩበት ሁኔታ ሊኖር አይገባም፤ የአፍሪካን ስም የሚሸከሙ መድረኮች የአፍሪካን ህዝብ ማንጸባረቅ አለባቸው” ሲል ምክር ቤቱ አክሎ ገልጿል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
የአኅጉሪቱን የኢነርጂ የወደፊት ሁኔታ ይወክላሉ በሚባሉ ሁነቶች ላይ የአፍሪካ ባለሙያዎች መገለላቸውን በመቃወም፣ በግንቦት ወር አጋማሽ በለንደን በሚካሄደው የአፍሪካ ኢነርጂ ጉባኤ ላይ ላለመሳተፍ መወሰኗን የጋና የኢነርጂ ምክር ቤት አስታዉቋል።
ምክር ቤቱ አዘጋጆቹ መለካት የሚችል የአካታችነት ማረጋገጫ እስኪያሳዩ ድረስ የአካባቢው ባለስልጣናት ተሳትፎአቸውን እንዲያጤኑት ጠይቋል። ይህም ሞዛምቢክን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ካስተላለፉት ተመሳሳይ ውሳኔ በመቀጠል የመጣ ነው።
“ጋና በአፍሪካ የኢነርጂ ታሪክ ውስጥ ተመልካች አይደለችም። ... አፍሪካ ለተሳትፎ ብቻ እንደ ገበያ የምትቆጠርበት እንዲሁም አፍሪካውያን በተግባራዊ አፈጻጸም ላይ እንደ አማራጭ ተሳታፊ የሚታዩበት ሁኔታ ሊኖር አይገባም፤ የአፍሪካን ስም የሚሸከሙ መድረኮች የአፍሪካን ህዝብ ማንጸባረቅ አለባቸው” ሲል ምክር ቤቱ አክሎ ገልጿል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X