ጥንታዊቷ የሐረር ከተማ በሩሲያ ሴንት ፒተርስበርግ ጉባኤ ላይ በደማቁ ተዘከረች

ጥንታዊቷ የሐረር ከተማ በሩሲያ ሴንት ፒተርስበርግ ጉባኤ ላይ በደማቁ ተዘከረች
ጥንታዊቷ የሐረር ከተማ በሩሲያ ሴንት ፒተርስበርግ ጉባኤ ላይ በደማቁ ተዘከረች  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 05.04.2026
ሰብስክራይብ
ጥንታዊቷ የሐረር ከተማ በሩሲያ ሴንት ፒተርስበርግ ጉባኤ ላይ በደማቁ ተዘከረች

መጋቢት 23 በሴንት ፒተርስበርግ በተከፈተውና “ሲቲዳል1.0” በተሰኘው አንደኛው ዓለም አቀፍ የአርኪኦሎጂ ጉባኤ ላይ የሐረሪ ክልል ባህል፣ ቅርጽና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሳሚ አብዱልዋሲ ጅብሪል ስለ ሐረር ከተማ ታሪክ የሚያሳይ ገለጻ አቅርበዋል፡፡

በአዲስ አበባ የሩሲያ የባሕል ማዕከል እንዳስታወቀው በገለጻው የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች፡-

ያለችበት ደረጃ፦ ከተማዋ በዩኔስኮ የተመዘገበች እና "አራተኛዋ የእስልምና ቅድስት ከተማ" መሆኗ ተብራርቷል፡፡

ሥነ-ሕንጻ፦ በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተገነባው የጀጎል ግንብ እና ከ80 በላይ ጥንታዊ መስጊዶች ዳሰሳ ተደርጓል።

ምርምር፦ ከአርኪኦሎጂ ቁፋሮዎች እና በሐረር ዙሪያ ካሉ የድንጋይ ላይ ሥዕሎች የተገኙ አዳዲስ መረጃዎች ቀርበዋል።

ከሩሲያ ጋር ስላለው ትስስር፦ ሩሲያዊው ገጣሚ እና ተጓዥ ኒኮላይ ጉሚሌቭ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ በሐረር የቆየ ሲሆን፣ የእሱ ጉዞዎች ለኢትዮጵያ ባህል ጥናት የነበረው ጠቃሚ አስተዋፅኦ ተነስቷል።

ታሪክ፦ ለበርካታ ምዕተ ዓመታት ከተማዋ በአፍሪካ ቀንድ የንግድ እና የሃይማኖት ማዕከል ሆና ማገልገሏ ተዘክሯል።

ጉባኤው የሐረርን ልዩ ባሕላዊ ቅርሶች ለማጥናትና ለመጠበቅ በሚደረገው ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ ትኩረት አድርጓል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0