የሞስኮ የንግድ ልዑክ በቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኢንቨስትመንት ዕድሎችን አጠና

የሞስኮ የንግድ ልዑክ በቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኢንቨስትመንት ዕድሎችን አጠና
የሞስኮ የንግድ ልዑክ በቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኢንቨስትመንት ዕድሎችን አጠና - Sputnik አፍሪካ, 1920, 05.04.2026
ሰብስክራይብ
የሞስኮ የንግድ ልዑክ በቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኢንቨስትመንት ዕድሎችን አጠና

ከ13 በላይ የሞስኮ ኩባንያዎችን ያቀፈ የሩሲያ የቢዝነስ ልዑካን ቡድን በቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢ እና መንግስት ያዘጋጀውን ማበረታቻ ገምግሟል።

ልዑኩ በተለይም በጤና፣ በፋርማሲዩቲካል፣ በሃይ-ቴክ እና በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ ሀብትና እውቀቱን ለማፍሰስ ያለውን ዝግጁነት መግለጹን የኢትዮጵያ የኢንስዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ገልጿል።

በተጨማሪም በዞኑ ውስጥ በምርት ላይ ከሚገኙ ባለሀብቶች ጋር በመወያየት በተግባር ያለውን የሥራ ሂደት የተመለከተ ሲሆን፣ ይህም የሩሲያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ መነሻ እንደሚሆን ተመልክቷል።

ልዑካኑ በመድኃኒት፣ በሕክምና ቴክኖሎጂዎች ምርት እና አቅርቦት ላይ ያተኮረው የሩሲያ እና የኢትዮጵያ ንግድ ፎረም እና ዐውደ ርዕይ ተሳታፊዎች ናቸው፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0