የሆሳዕና በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በድምቀት ተከበረ

ሰብስክራይብ
የሆሳዕና በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በድምቀት ተከበረ

በአገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በሚገኙ ሁሉም አብያተክርስቲያናት የሚከበረው በዓሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅርና ትሕትናውን ለመግለጽ በአህያ ውርንጭላ ላይ ተጭኖ በክብር ወደ ኢየሩሳሌም መግባቱን የሚዘክር ሲሆን፣ የዐቢይ ጾም 8ኛ ሳምንት መጠሪያ ነው።

ምዕመናን በዓሉን የዘንባባ ዝንጣፊዎችን በመያዝ "ሆሳዕና በአርያም" እያሉ በማመስገን እና ዝንጣፊውን በራሳቸው ላይ በማሰር በሃይማኖታዊ ስርዓት አክብረዋል።

ይህ በዓል ነገ ሰኞ የሚጀመረውንና በጾምና በስግደት የሚታሰበውን የእየሱስ ክርስቶስ የሕማማት ሳምንት በይፋ እንደሚጀምርም ያበስራል።

ቪዲዮ፦ 1 በስፑትኒክ አፍሪካ ባልደረባ፣ 2 እና 3 ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኙ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0