በመሃል ቴል አቪቭ የፀረ-ጦርነት ሰልፍ ተካሄደ፤ የእስራኤል ፖሊስ ሰልፈኞቹን በትኗል

ሰብስክራይብ

በመሃል ቴል አቪቭ የፀረ-ጦርነት ሰልፍ ተካሄደ፤ የእስራኤል ፖሊስ ሰልፈኞቹን በትኗል

​በመቶዎች የሚቆጠሩ እስራኤላውያን በቲያትር አደባባይ ተሰባስበው በእስራኤል ላይ የጦር መሳሪያ ማዕቀብ እንዲጣል እንዲሁም በኢራን፣ በሊባኖስ እና በጋዛ ሰርጥ የሚካሄዱ ወታደራዊ ዘመቻዎች እንዲቆሙ ጠይቀዋል።

​ ቆየት ብሎም የእስራኤል ፖሊስ ስብሰባውን መበተን የጀመረ ሲሆን፣ በሕግ አስከባሪዎችና በተቃዋሚዎች መካከል ግጭት መፈጠሩን በስፍራው የተገኘው የስፑትኒክ ዘጋቢ ገልጿል።

​ሰልፉ በመንግስት የፈቃድ ማረጋገጫ ተሰጥቶት የነበረ ቢሆንም፣ በአየር  ጥቃት ስጋት ምክንያት በክፍት ቦታዎች ከ50 በላይ ሰዎች መሰብሰብን የሚከለክለውን የሲቪል መከላከያ አገልግሎት ደንብ ጥሷል ተብሏል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0