የኦርቶዶክስ ምሁር ክርስቲያን ጽዮናውያን ስለ አዲሱ የመካከለኛው ምስራቅ የመስቀል ጦርነት ለምን ይህን ያህል ቀናኢ እንደሆኑ አብራሩ
10:48 05.04.2026 (የተሻሻለ: 10:58 05.04.2026)

ሰብስክራይብ
የኦርቶዶክስ ምሁር ክርስቲያን ጽዮናውያን ስለ አዲሱ የመካከለኛው ምስራቅ የመስቀል ጦርነት ለምን ይህን ያህል ቀናኢ እንደሆኑ አብራሩ
የክርስቲያን ጽዮናዊነት የበቀለበት የፕሮቴስታንት እምነት "ለመከፋፈል፣ ለዶክትሪን ለውጥ እና ለአዳዲስ ሀሳቦች መፈጠር የተጋለጠ" ሲሆን፣ አንዳንዶቹ ዘርፎች "ወደ ይሁዲነት በጣም በመቅረብ "የአንግሎ-እስራኤሊዝምን ዶክትሪን (አስተምህሮ) እና የ"ይሁዲ-ክርስቲያን" ድብልቅ ሃይማኖታዊ ንቅናቄን ፈጥረዋል ሲሉ የሞስኮ ስቴት ሊንጉዊስቲክ ዩኒቨርሲቲ የቲዎሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ፕሮፌሰር ሮማን ሲላንትዬቭ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
“የፕሮቴስታንት፣ በተለይም የአሜሪካ ፕሮቴስታንት አጠቃላይ ባህሪ ወደ ብሉይ ኪዳን በእጅጉ ያዘነበለ ነው። ኦርቶዶክስ ግን ከሁሉ አስቀድሞ የሐዲስ ኪዳን ሃይማኖት ናት” ሲሉ ሲላንትየቭ አብራርተዋል።
በኦርቶዶክሳዊነት ውስጥ “ሁሉም አስፈላጊ ዶክትሪኖች ከረጅም ጊዜ በፊት በሰባቱ የኢኩሜኒካል ጉባኤያት ተደንግገዋል፤ ከዚህ ውጪ ያለ ማንኛውም ነገር እውቅና የለውም።
ኦርቶዶክስ በአስተምህሮ ወላዋይነት እና መለዋወጥ አትታወቅም። እነዚህ ጉዳዮች በሙሉ ከሺህ ዓመታት በፊት እልባት አግኝተዋል፡፡” ሲሉ ምሁሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።
እንደ ሲላንትዬቭ ገለጻ፣ ኦርቶዶክስ የክርስቲያን ጽዮናዊነትን ውድቅ የምታደርግ ሲሆን፣ እሱን እና ፕሮቴስታንቲዝምን በአጠቃላይ “በመሠረቱ አንድ ትልቅ ክህደት” አድርጋ ትቆጥራለች።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
የክርስቲያን ጽዮናዊነት የበቀለበት የፕሮቴስታንት እምነት "ለመከፋፈል፣ ለዶክትሪን ለውጥ እና ለአዳዲስ ሀሳቦች መፈጠር የተጋለጠ" ሲሆን፣ አንዳንዶቹ ዘርፎች "ወደ ይሁዲነት በጣም በመቅረብ "የአንግሎ-እስራኤሊዝምን ዶክትሪን (አስተምህሮ) እና የ"ይሁዲ-ክርስቲያን" ድብልቅ ሃይማኖታዊ ንቅናቄን ፈጥረዋል ሲሉ የሞስኮ ስቴት ሊንጉዊስቲክ ዩኒቨርሲቲ የቲዎሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ፕሮፌሰር ሮማን ሲላንትዬቭ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
“የፕሮቴስታንት፣ በተለይም የአሜሪካ ፕሮቴስታንት አጠቃላይ ባህሪ ወደ ብሉይ ኪዳን በእጅጉ ያዘነበለ ነው። ኦርቶዶክስ ግን ከሁሉ አስቀድሞ የሐዲስ ኪዳን ሃይማኖት ናት” ሲሉ ሲላንትየቭ አብራርተዋል።
በኦርቶዶክሳዊነት ውስጥ “ሁሉም አስፈላጊ ዶክትሪኖች ከረጅም ጊዜ በፊት በሰባቱ የኢኩሜኒካል ጉባኤያት ተደንግገዋል፤ ከዚህ ውጪ ያለ ማንኛውም ነገር እውቅና የለውም።
ኦርቶዶክስ በአስተምህሮ ወላዋይነት እና መለዋወጥ አትታወቅም። እነዚህ ጉዳዮች በሙሉ ከሺህ ዓመታት በፊት እልባት አግኝተዋል፡፡” ሲሉ ምሁሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።
እንደ ሲላንትዬቭ ገለጻ፣ ኦርቶዶክስ የክርስቲያን ጽዮናዊነትን ውድቅ የምታደርግ ሲሆን፣ እሱን እና ፕሮቴስታንቲዝምን በአጠቃላይ “በመሠረቱ አንድ ትልቅ ክህደት” አድርጋ ትቆጥራለች።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X