ኢራን ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር ሰላም ለመፍጠር ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጣለች - ዲፕሎማሲያዊ ምንጭ
14:50 04.04.2026 (የተሻሻለ: 15:36 04.04.2026)

ሰብስክራይብ
ኢራን ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር ሰላም ለመፍጠር ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጣለች - ዲፕሎማሲያዊ ምንጭ
በቴሕራን የሚገኝ አንድ ዲፕሎማሲያዊ ምንጭ ለስፑትኒክ እንደገለጸው፣ ኢራን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የጠየቀቻቸው ነጥቦች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦
ባለፉት ጊዜያት ካጋጠሙ "መራራ ተሞክሮዎች" በመነሳት፣ የተኩስ አቁም ብቻ ሳይሆን በቀጣናው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፣
ወራሪዎች በግልጽ እንዲኮነኑ፣
ለደረሰው ቁሳዊ ጉዳት ካሳ እና የጉዳት ክፍያ እንዲፈጸም፣
በኢራን ላይ የተጣሉ ማዕቀቦች በሙሉ በሙሉ እንዲነሱ እና
ኢራን ለሰላማዊ ዓላማ የኑክሌር ፕሮግራም የመገንባት መብቷ እንዲከበር።
ግጭቱ ከተጀመረ አንስቶ አሜሪካ ተደጋጋሚ ጥያቄ ብታቀርብም፣ በቴሕራን እና በዋሽንግተን መካከል እስካሁን ምንም ዓይነት ቀጥተኛ ድርድር እንዳልተደረገ ምንጩ አክሎ ገልጿል።
የኢራን ባለሥልጣናት ዋሽንግተን ለመነጋገር ፍላጎት እንዳላት የሚገልጹ መልዕክቶችን በአሸማጋዩች በኩል መቀበላቸውን ቢያረጋግጡም፣ ማንኛውንም ዓይነት ቀጥተኛ ንግግር ግን አስተባብለዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
በቴሕራን የሚገኝ አንድ ዲፕሎማሲያዊ ምንጭ ለስፑትኒክ እንደገለጸው፣ ኢራን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የጠየቀቻቸው ነጥቦች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦
ባለፉት ጊዜያት ካጋጠሙ "መራራ ተሞክሮዎች" በመነሳት፣ የተኩስ አቁም ብቻ ሳይሆን በቀጣናው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፣
ወራሪዎች በግልጽ እንዲኮነኑ፣
ለደረሰው ቁሳዊ ጉዳት ካሳ እና የጉዳት ክፍያ እንዲፈጸም፣
በኢራን ላይ የተጣሉ ማዕቀቦች በሙሉ በሙሉ እንዲነሱ እና
ኢራን ለሰላማዊ ዓላማ የኑክሌር ፕሮግራም የመገንባት መብቷ እንዲከበር።
ግጭቱ ከተጀመረ አንስቶ አሜሪካ ተደጋጋሚ ጥያቄ ብታቀርብም፣ በቴሕራን እና በዋሽንግተን መካከል እስካሁን ምንም ዓይነት ቀጥተኛ ድርድር እንዳልተደረገ ምንጩ አክሎ ገልጿል።
የኢራን ባለሥልጣናት ዋሽንግተን ለመነጋገር ፍላጎት እንዳላት የሚገልጹ መልዕክቶችን በአሸማጋዩች በኩል መቀበላቸውን ቢያረጋግጡም፣ ማንኛውንም ዓይነት ቀጥተኛ ንግግር ግን አስተባብለዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X