ሞሮኮ በ2026 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት 4.3 ሚሊዮን ቱሪስቶችን አስተናገደች፤ ካለፈው ዓመት የ7% ጭማሪ አለው - የቱሪዝም ሚኒስቴር

ሰብስክራይብ
ሞሮኮ በ2026 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት 4.3 ሚሊዮን ቱሪስቶችን አስተናገደች፤ ካለፈው ዓመት የ7% ጭማሪ አለው - የቱሪዝም ሚኒስቴር

ሚኒስቴሩ በመግለጫዉ እንዳስታወቀው፣ በሞሮኮ የቱሪስቶች ቁጥር በመጋቢት ወር በ18 በመቶ የጨመረ ሲሆን ለዚህም እንደ ምክንያት የተጠቀሱት፦

🟠 የተሻሻለ የአየር ትራንስፖርት ትስስር፣

🟠 የተለያዩ የቱሪስት ምንጭ ገበያዎች መኖራቸው እና

🟠ማራኪ እና የተሻሻሉ የቱሪዝም አገልግሎቶች ናቸው።

​የውጭ ምንዛሪ መረጃዎች እንደሚያሳዩት፥ እስከ መጋቢት ወር መጀመሪያ ድረስ ከቱሪዝም የተገኘው ገቢ 2.3 ቢሊዮን ዶላር የደረሰ ሲሆን ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ22.2 በመቶ እድገት አሳይቷል።

​ሀገሪቱ እ.ኤ.አ. በ2030 ከስፔን እና ከፖርቱጋል ጋር በመሆን የፊፋ የዓለም ዋንጫን በጋራ ስታስተናግድ 26 ሚሊዮን ጎብኚዎችን ለመሳብ አልማለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0