ሩሲያ ምርጥ የትራንስፖርት ተሞክሮዎቿን ለአፍሪካ ለማካፈል ተዘጋጅታለች - የትራንስፖርት ሚኒስቴር
ሩሲያ ምርጥ የትራንስፖርት ተሞክሮዎቿን ለአፍሪካ ለማካፈል ተዘጋጅታለች - የትራንስፖርት ሚኒስቴር
አፍሪካ በዓለም ላይ በፍጥነት እያደጉ ካሉ ቀጣናዎች ውስጥ አንዷ ናት፤ ነገር ግን ቀጣይነት ያለው ኢኮኖሚያዊ ዕድገቷ በአኅጉሪቱ ላይ ዘመናዊ እንዲሁም ሉዓላዊ የትራንስፖርት እና የሎጂስቲክስ ትስስር በመገንባት ላይ የተመሠረተ መሆኑን የሩሲያ የትራንስፖርት ሚኒስትር በዓለም አቀፍ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ፎረም ላይ ለስፑትኒክ ገልፀዋል።
ይህ የትራንስፖርት ሥርዓት የሚከተሉትን ማካተት ይኖርበታል፦
🟠 ሁለገብ የትራንስፖርት ኮሪደሮች፣
🟠 ዲጂታል የጭነት እንቅስቃሴ አስተዳደር ሥርዓቶች እና
🟠 የሎጂስቲክስ ማዕከላት።
የሩሲያ ምድር ባቡር፣ ፌስኮ እና አቭቶቫዝ ጨምሮ የሩሲያ ኩባንያዎች በአስቸጋሪ የአየር ንብረት እና የጂኦሎጂካል ሁኔታዎች ውስጥ የትራንስፖርት መሠረተ ልማት እና ዲጂታል መፍትሄዎችን በመፍጠር እና በማንቀሳቀስ ረገድ ልዩ ልምድ እንዳላቸው ሚኒስቴሩ አመላክቷል።
በተጨማሪም፣ የሎሜ የራስ ገዝ ወደብ ጠቅላላ ዳይሬክቶሬት ተወካይ ክዋሜ ቱና ዊሊ ኔኔ፣ የአፍሪካ አገራት ከሩሲያ ጋር ቀጥተኛ የአየር በረራ ግንኙነት ለመመሥረት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል። ሞስኮ ለሁሉም ወገን ጠቃሚ ለሆነ ትብብር የሚያገለግል "ሁሉንም አሸናፊ ካርዶች" በእጇ ይዛለች ሲሉ አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X