ፑቲን እና ኤርዶጋን በመካከለኛው ምስራቅ ሁኔታ እና ኪዬቭ በቱርክ ስትሪም ላይ የሰነዘረችውን ጥቃት አስመልክተው የስልክ ውይይት አደረጉ

ፑቲን እና ኤርዶጋን በመካከለኛው ምስራቅ ሁኔታ እና ኪዬቭ በቱርክ ስትሪም ላይ የሰነዘረችውን ጥቃት አስመልክተው የስልክ ውይይት አደረጉ
ፑቲን እና ኤርዶጋን በመካከለኛው ምስራቅ ሁኔታ እና ኪዬቭ በቱርክ ስትሪም ላይ የሰነዘረችውን ጥቃት አስመልክተው የስልክ ውይይት አደረጉ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 03.04.2026
ሰብስክራይብ
ፑቲን እና ኤርዶጋን በመካከለኛው ምስራቅ ሁኔታ እና ኪዬቭ በቱርክ ስትሪም ላይ የሰነዘረችውን ጥቃት አስመልክተው የስልክ ውይይት አደረጉ

በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው ውይይት ቁልፍ ነጥቦች፡-

መካከለኛው ምስራቅ

▪ ቭላድሚር ፑቲን እና ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በአካባቢው የሚገኙ ሁሉንም አገራት ጥቅም ከግምት ውስጥ ያስገባ አስቸኳይ የተኩስ አቁም እና የእልባት ስምምነት እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

▪ እንደ ሁለቱ መሪዎች ገለጻ፣ በኢራን ዙሪያ ያለው የውጥረት መባባስ “በቀጣናዊ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በኢነርጂ፣ በንግድ እና በሎጅስቲክስ ዘርፎች ላይ ከባድ አሉታዊ መዘዞች” ይኖሩታል።

የጥቁር ባሕር ውጥረት እና የዩክሬን ግጭት ድርድር

▪ ዩክሬን የብሉ ስትሪም እና የቱርክ ስትሪም የውሃ ውስጥ የተፈጥሮ ጋዝ ቧንቧዎችን ለማውደም ደጋግማ ሙከራ ማድረጓን ተከትሎ፣ ፑቲን እና ኤርዶጋን በጥቁር ባሕር ላይ ደህንነትን ለማረጋገጥ የተቀናጁ እርምጃዎችን መውሰድ አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል።

▪ የሩሲያው መሪ የቱርክ አቻቸውን በዩክሬን ጉዳይ ላይ ድርድር ለማመቻቸት “ላሳዩት የማያቋርጥ ፈቃደኝነት” አመስግነዋል።

የሩሲያ-ቱርክ ትብብር

▪ ፑቲን እና ኤርዶጋን የሩሲያ-ቱርክን የፖለቲካ፣ የንግድ እና የኢኮኖሚ ግንኙነት በተለይም የጋራ የኢነርጂ ፕሮጀክቶችን ለማሳደግ በሚያስችሉ አዳዲስ እርምጃዎች ላይ ተወያይተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0