ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር በዕዳ አያያዝ ዙሪያ ስምምነት ላይ ደርሳለች - የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስቴር
19:10 03.04.2026 (የተሻሻለ: 19:18 03.04.2026)

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር በዕዳ አያያዝ ዙሪያ ስምምነት ላይ ደርሳለች - የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስቴር
ስምምነቱ የተደረሰው በቻይና በተካሄደው የሀገራቱ የገንዘብ ሚኒስትሮች ስብሰባ ወቅት መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡ ውይይቱ የዕዳ ሽግሽግን፣ በመካሄድ ላይ ያሉ ፕሮጀክቶች አፈጻጸምን፣ አዳዲስ የፋይናንስ ዕድሎችን እንዲሁም የአዲሱን የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ልማት ዕቅዶችን ያካተተ እንደነበር ገልጿል፡፡
የውይይቱ ዋና ውጤቶች፦
የዕዳ ሽግሽግ ስምምነት
ሁለቱ ወገኖች በዕዳ አያያዝ ዙሪያ መፍትሄ ላይ የደረሱ ሲሆን፣ በቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ መሠረት የሁለትዮሽ ስምምነቱን ለመፈረም ተስማምተዋል።
በሂደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችን ማፋጠን
ነባር ፕሮጀክቶች በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ የገንዘብ ክፍያ ሂደትን እና ቅንጅትን ለማሻሻል ስምምነት ላይ ተደርሷል።
ለስትራቴጂካዊ ፕሮጀክቶች አዲስ ፋይናንስ
ሚኒስትሮቹ ዓለም አቀፍ ንግድን ለማሳደግ ለሚገነባው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ ለቀዳሚ መሠረተ ልማቶች አዲስ የገንዘብ ድጋፍ ስለሚያገኙበት ሁኔታ ተወያይተዋል።
“በስብሰባው ላይ የተደረሰው መግባባት በሁለትዮሽ ግንኙነታችን ውስጥ ወሳኝ ወቅት ነው። የሁለቱን ሀገራት ጥቅም የሚያስጠብቅ ዘላቂ አጋርነት ለማግኘት ከቻይና አጋሮቻችን ጋር በቅርበት ለመሥራት ቁርጠኞች ነን” ሲሉ የኢትዮጵያ ፋይናንስ ሚኒስትር አሕመድ ሸዴ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ለቻይና መንግሥት የምትከፍለውን የ5.38 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ በከፊል ወደ ቻይና ገንዘብ (ዩዋን) ለመቀየር ንግግር መጀመሯ ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
ስምምነቱ የተደረሰው በቻይና በተካሄደው የሀገራቱ የገንዘብ ሚኒስትሮች ስብሰባ ወቅት መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡ ውይይቱ የዕዳ ሽግሽግን፣ በመካሄድ ላይ ያሉ ፕሮጀክቶች አፈጻጸምን፣ አዳዲስ የፋይናንስ ዕድሎችን እንዲሁም የአዲሱን የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ልማት ዕቅዶችን ያካተተ እንደነበር ገልጿል፡፡
የውይይቱ ዋና ውጤቶች፦
የዕዳ ሽግሽግ ስምምነት
ሁለቱ ወገኖች በዕዳ አያያዝ ዙሪያ መፍትሄ ላይ የደረሱ ሲሆን፣ በቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ መሠረት የሁለትዮሽ ስምምነቱን ለመፈረም ተስማምተዋል።
በሂደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችን ማፋጠን
ነባር ፕሮጀክቶች በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ የገንዘብ ክፍያ ሂደትን እና ቅንጅትን ለማሻሻል ስምምነት ላይ ተደርሷል።
ለስትራቴጂካዊ ፕሮጀክቶች አዲስ ፋይናንስ
ሚኒስትሮቹ ዓለም አቀፍ ንግድን ለማሳደግ ለሚገነባው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ ለቀዳሚ መሠረተ ልማቶች አዲስ የገንዘብ ድጋፍ ስለሚያገኙበት ሁኔታ ተወያይተዋል።
“በስብሰባው ላይ የተደረሰው መግባባት በሁለትዮሽ ግንኙነታችን ውስጥ ወሳኝ ወቅት ነው። የሁለቱን ሀገራት ጥቅም የሚያስጠብቅ ዘላቂ አጋርነት ለማግኘት ከቻይና አጋሮቻችን ጋር በቅርበት ለመሥራት ቁርጠኞች ነን” ሲሉ የኢትዮጵያ ፋይናንስ ሚኒስትር አሕመድ ሸዴ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ለቻይና መንግሥት የምትከፍለውን የ5.38 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ በከፊል ወደ ቻይና ገንዘብ (ዩዋን) ለመቀየር ንግግር መጀመሯ ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X