ማዳጋስካር ከሩሲያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር በግብርና፣ በኢነርጂ እና በማዕድን ዘርፎች ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየሰራች መሆኑን አስታወቀች

ሰብስክራይብ

ማዳጋስካር ከሩሲያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር በግብርና፣ በኢነርጂ እና በማዕድን ዘርፎች ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየሰራች መሆኑን አስታወቀች

"የሩሲያ ፌዴሬሽን ሁልጊዜም ለማዳጋስካር ቅርብ ነው፤ በጋራ ፍላጎቶች ላይ የተመሠረተውን ግንኙነታችንንም ማሳደጋችንን እንቀጥላለን" ሲሉ የማዳጋስካር ጠቅላይ ሚኒስትር ማሚቲያና ራጃኦናሪሰን ለሩሲያ የዜና ወኪል ተናግረዋል፡፡

​ ማዳጋስካር የሩሲያ ባለሀብቶችን በዋና ዋና የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ለማሳተፍ እንደምትፈልግም ገልፀዋል።

"ሁለቱም ሀገራት ፍላጎቶቻቸውን ማሳካት እንዲችሉ ትብብራችንን እናጠናክራለን" በማለት አክለዋል፡፡

​ በትናንትናው ዕለት ራጃኦናሪሰን የሩሲያ ልዑካንን የተቀበሉ ሲሆን፣ ይህም አዲሱ የማዳጋስካር አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር በስልጣን ዘመናቸው ከተቀበሏቸው የመጀመሪያዎቹ የውጭ ሀገር ልዑካን መካከል አንዱ ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0