የኢትዮጵያና ታንዛኒያ ወታደራዊ ትብብር መጠናከር ለቀጣናው የጋራ የደህንነት ጋሻ ነው – ታንዛኒያዊ ባለሙያ
18:24 03.04.2026 (የተሻሻለ: 18:38 03.04.2026)

ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያና ታንዛኒያ ወታደራዊ ትብብር መጠናከር ለቀጣናው የጋራ የደህንነት ጋሻ ነው – ታንዛኒያዊ ባለሙያ
የጋራ ወታደራዊ ሥልጠና፣ ሽብርተኝነት እና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ የተቀናጁ ዘመቻዎችን፣ የባሕር ላይ ደህንነት፣ የወታደራዊ ቴክኖሎጂዎች፣ የክትትል ስርዓቶች እና የሳይበር ደህንነት በወታደራዊ ስምምነቱ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚችሉ ጉዳዮች መሆናችውን የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ተንታኝ አብዱልናስር ምዊታ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
"የመረጃ ክፍተቶችን መሙላት በቅጽበታዊ ልውውጥ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓቶችን ያጠናክራል። ውስብስብ ውጥረት ባለበት በዚህ ቀጣና ውስጥ ወታደራዊ መተማመንን መገንባት እጅግ ወሳኝ ነው።"
በሃገራቱ መካከል የተደረጉ ውይይቶች ልማዳዊ ዲፕሎማሲ ብቻ ሳይሆኑ ስልታዊ የደህንነት መንገዶች እንደመሆናቸው በደህንነት ስጋቶች ላይ በጋራ መንቀሳቀስ እንዲጀምሩ ያደርጋል ሲሉም አስረድተዋል፡፡
“ምስራቅ አፍሪካ እና የአፍሪካ ቀንድ እንደ ሽብርተኝነት፣ ግጭቶች፣ የድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች እና የጦር መሣሪያ እና የሰዎች ዝውውር ያሉ ስጋቶች ይጋረጡባቸዋል። ይህ አጋርነት ስጋቶችን በጋራ የመረጃ መረቦች ቀድሞ ለመገታት ይችላል” ብለዋል፡፡
እንደባለሙያው ገለጻ፣ ይህ ወታደራዊ አጋርነት በቀጣናው ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ይጠበቃል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
የጋራ ወታደራዊ ሥልጠና፣ ሽብርተኝነት እና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ላይ የተቀናጁ ዘመቻዎችን፣ የባሕር ላይ ደህንነት፣ የወታደራዊ ቴክኖሎጂዎች፣ የክትትል ስርዓቶች እና የሳይበር ደህንነት በወታደራዊ ስምምነቱ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚችሉ ጉዳዮች መሆናችውን የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ተንታኝ አብዱልናስር ምዊታ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
"የመረጃ ክፍተቶችን መሙላት በቅጽበታዊ ልውውጥ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓቶችን ያጠናክራል። ውስብስብ ውጥረት ባለበት በዚህ ቀጣና ውስጥ ወታደራዊ መተማመንን መገንባት እጅግ ወሳኝ ነው።"
በሃገራቱ መካከል የተደረጉ ውይይቶች ልማዳዊ ዲፕሎማሲ ብቻ ሳይሆኑ ስልታዊ የደህንነት መንገዶች እንደመሆናቸው በደህንነት ስጋቶች ላይ በጋራ መንቀሳቀስ እንዲጀምሩ ያደርጋል ሲሉም አስረድተዋል፡፡
“ምስራቅ አፍሪካ እና የአፍሪካ ቀንድ እንደ ሽብርተኝነት፣ ግጭቶች፣ የድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች እና የጦር መሣሪያ እና የሰዎች ዝውውር ያሉ ስጋቶች ይጋረጡባቸዋል። ይህ አጋርነት ስጋቶችን በጋራ የመረጃ መረቦች ቀድሞ ለመገታት ይችላል” ብለዋል፡፡
እንደባለሙያው ገለጻ፣ ይህ ወታደራዊ አጋርነት በቀጣናው ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ይጠበቃል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X