- Sputnik አፍሪካ, 1920
Sovereignty Sources
ዓለም በሉላዊነት ምክንያት ስትተሳሰር ፤ ፕሮግራሙም አፍሪካ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ኃብት፣ በማደግ ላይ ባለው የሕዝብ ቁጥሯ ፣ በወጣት ኃይሏ እና በአህጉሪቱ ባሉ አዳዲስ ግኝቶችና የመፍትሄ ሃሳቦች ያላትን የመወዳደር አቅምና ጥቅም በሰፊው ይዳስሳል፡፡ እንኳን ወደ 'ሶቨርኒቲ ሶርስ' ፕሮግራም በደህና መጡ፣

የኦቲዝም ቀን በኢትዮጵያ፦ ማኅበራዊ መገለልን ድል የነሳው የ24 ዓመታት የጽናት ጉዞ

የኦቲዝም ቀን በኢትዮጵያ፦ ማኅበራዊ መገለልን ድል የነሳው የ24 ዓመታት የጽናት ጉዞ
ሰብስክራይብ

"ልጄ 10 ዓመት እስኪሞላት ድረስ እናቴ ከሶፋ ጋር እያሰረችልኝ እኔ መስተንግዶ እሰራ ነበር። 'ከእሷ ጋር አትሁኑ' ተብዬ ለማኅበረሰቡ መጥፎ ምሳሌ ተደርጌ ነበር፤ 'ትምህርት ያቆመችው እንዲህ ዓይነት ልጅ ወልዳ ነው' ይባላል። ጫናው እናቴን እስከመጨረሻው መቃብር ውስጥ እስኪከታት ደርሶ ነበር። [...] መጀመሪያ 'ከእሷ ጋር አትሁኑ' ተብዬ ለማኅበረሰቡ መጥፎ ምሳሌ ተደርጌ ነበር። ዛሬ ግን ልጄ ቦርሳዋን አዝላ ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ እናቴ 'በቃ ልጄ ዛሬ ከበሽታ ድናለች' ብላ ተደሰተች።አሁን ከአሁን በኋላ ምንም እስራት የለብኝም፤ እንደ ልጅነቴ መስራት፣ መማርና የምፈልገውን መሆን እንደምችል አውቄያለሁ።" — ስትል የኦቲዝም ያለባት ልጅ ወላጅ እናት የሺእመቤት ዘለቀ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግራለች ።

በዚህ የ ሶቨርኒቲ ሶርስስ በልዩ መሠናዶው በኢትዮጵያ ዛሬ መጋቢት 24 ስለሚከበረው የዓለም የኦቲዝም ቀን ከእሌኒ ዳምጠው፣ የኒያ ፋውንዴሽን ጆይ ኦቲዝም ማዕከል ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ አዜብ ገ/ስላሴ በማዕከሉ መምህር እንዲሁም የሺዕመቤት ዘለቀ፣ ከኦቲዝም ጋር አብራ የምትኖር ልጅ እናት ጋር ተወያይተናል።
ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezer Spotify Podcast AddictPocket CastsAfripodsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0