ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የዶሜ ገሮ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ተመረቀ

ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የዶሜ ገሮ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ተመረቀ
ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የዶሜ ገሮ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ተመረቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 02.04.2026
ሰብስክራይብ
ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የዶሜ ገሮ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ተመረቀ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን በሳላማጎ ወረዳ የተገነባው የፀሐይ ኃይል ማመንጫ፣ 625 ኪሎ ዋት በማመንጨት ከ6ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ለመጪዎቹ 20 ዓመታት የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የሚኒስቴሩ የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ሱልጣን ወሊ፣ በገጠራማ አካባቢዎች የሚኖሩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ በአደሌ ፕሮጀክት ከዓለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ብድር በክልሉ ለመገንባት ከታሰቡት ዘጠኝ ፕሮጀክቶች ሰባቱ ተጠናቀው አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ |
አዳዲስ ዜናዎች
0