ኢትዮጵያ የታንዛኒያን አየር ኃይል ለማጠናከር ድጋፍ ለልታደርግ ነው - መከላከያ ሠራዊት

ኢትዮጵያ የታንዛኒያን አየር ኃይል ለማጠናከር ድጋፍ
 ኢትዮጵያ የታንዛኒያን አየር ኃይል ለማጠናከር ድጋፍ  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 02.04.2026
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የታንዛኒያን አየር ኃይል ለማጠናከር ድጋፍ ለልታደርግ ነው - መከላከያ ሠራዊት

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ያለውን ሰፊ ልምድና ጠንካራ አቅም በመጠቀም፣ የታንዛኒያን አየር ኃይል በሁሉም ዘርፎች ለመገንባት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ በዳሬሰላም በተካሄደው የኢትዮጵያ–ታንዛኒያ የጋራ መከላከያ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ተገልጿል፡፡

በተለይም ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ የመከላከያ የልህቀት ማዕከላት የሰለጠኑና አሁንም በስልጠና ላይ ያሉ የታንዛኒያ ወታደራዊ መኮንኖችና ሙያተኞች፣ የሁለቱ አገራት ወታደራዊ ትስስር ማሳያ ሆነው ቀርበዋል ሲል የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አስታውቋል።

የታንዛኒያ የመከላከያ ዘመቻና ስልጠና ኃላፊ ሜጀር ጄኔራል ኢብራሂም ሚካኤል ምሆና፣ ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ መከላከያ ሠራዊት በስልጠና ዘርፍ የምታደርገው ድጋፍ ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0