"የደቡባዊ አፍሪካ ልማት ማኅበረሰብ የራሱ ባንክ ሊኖረው ይገባል" - የዚምባብዌ ባለሥልጣን

ሰብስክራይብ
"የደቡባዊ አፍሪካ ልማት ማኅበረሰብ የራሱ ባንክ ሊኖረው ይገባል" - የዚምባብዌ ባለሥልጣን

​ እንዲህ ዓይነቱ የፋይናንስ መዋቅር የንግድ ልውውጥን ለማሳለጥ እና ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር ወሳኝ የሆነውን የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ለማዘመን ይረዳል ሲሉ የዚምባብዌ የዕዳ እና ልማት ጥምረት ዳይሬክተር ጆን ማኬቶ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

​ከባድ ጭነቶችን ከየብስ መንገድ ወደ ባቡር ትራንስፖርት ማዛወር የመንገድ መሠረተ ልማቶችን ዕድሜ ከማራዘሙ ባለፈ፣ በቀጣናው ለሚታለመው ሰፊ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እንደ ዋነኛ ሞተር ያገለግላል ብለዋል።


"የባቡር መስመር በማንኛውም የዓለም ክፍል፣ በተለይም በደቡባዊ አፍሪካ፣ ለኢኮኖሚ ልማት እጅግ አስፈላጊ አነቃቂ መሣሪያ ነው" ሲሉ አስረድተዋል።


​በባቡር መስመር እና በወደብ ማስፋፊያ ላይ የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች ከሎጂስቲክስ መሻሻል ባለፈ "ድንበር የለሽ ቀጣና" ለመፍጠር መሠረት መሆናቸውን ማኬቶ አብራርተዋል።

​የደቡባዊ አፍሪካ የልማት ማኅበረሰብ ለሸቀጦች እና ለሰዎች ምቹ የሆኑ የመጓጓዣ ኮሪደሮችን በመፍጠር፣ በድንበር ፍተሻ ጣቢያዎች ላይ የሚባክነውን ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ እንዲሁም የአነስተኛ ነጋዴዎችንና የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት ማሻሻል እንደሚችልም አመላክተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0