የ1,200 የከተማ አውቶብሶች የናፍጣ ሞተር በተፈጥሮ ጋዝ ሞተር ሊተካ ነው

የከተማ አውቶብሶች
የከተማ አውቶብሶች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 01.04.2026
ሰብስክራይብ
የ1,200 የከተማ አውቶብሶች የናፍጣ ሞተር በተፈጥሮ ጋዝ ሞተር ሊተካ ነው

እርምጃው የሀገሪቱን የተፈጥሮ ጋዝ ሀብት በመጠቀም ለነዳጅ የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪ ለመቀነስ ያለመ ነው ተብሏል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት፤ በቃሊቲ ቅርንጫፉ የሞተር መተኪያ ማዕከልና የጋዝ መሙያ ማደያ ግንባታ ተጠናቆ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንደተገባ እና ለሙከራ የሚሆኑ ሞተሮች ተከላ እንደተከናወነ አስታውቋል።

‍ የድርጅቱ የቴክኒክ ባለሙያዎችም ስለ አዲሱ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምና ጥገና ሥልጠና በመውሰድ ላይ ናቸው መባሉን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡

በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0