ደቡብ አፍሪካ "የሀገሪቱ የንግድ ተቋማት ወደ ኋላ እንዳይቀሩ" ከባለሀብቶች ጋር በቅርበት ትሠራለች - ሚኒስትር

ሰብስክራይብ

ደቡብ አፍሪካ "የሀገሪቱ የንግድ ተቋማት ወደ ኋላ እንዳይቀሩ" ከባለሀብቶች ጋር በቅርበት ትሠራለች - ሚኒስትር

‍ በደቡብ አፍሪካ ከተካሄደው የኢንቨስትመንት ኮንፈረንስ ጎን ለጎን ሀሳባቸው ያካፈሉት የአነስተኛ ንግዶች ሚኒስትር ስቴላ ንዳቤኒ-አብራሃምስ፤ ወደ ሀገሪቱ ስለሚገባው ካፒታል ያላቸውን ተስፋ ሲገልጹ "ተጨማሪ ቢሊዮን ራንዶች... ወደ ሀገራችን እየመጡ ነው" ብለዋል። ይህም አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር መንገድ እንደሚከፍት ጠቁመዋል።

መንግሥት የኢንቨስትመንት ተጠቃሚነትን ሁሉን አቀፍ ለማድረግ ከባለሀብቶች ጋር በቅርበት እንደሚሠራ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ንዳቤኒ-አብራሃምስ አክለውም የሰው ሠራሽ አስተውህሎት የመረጃ ማዕከላት፣ የተሻሻለ የኢንተርኔት ተደራሽነት እና የንግድ ተቋማት እርስ በርስ የንግድ ልውውጥ የሚያደርጉባቸውን መድረኮች ጨምሮ በዲጂታል ዕድገት ላይ ትኩረት መደረጉን ገልጸዋል። ይህም በአጠቃላይ የኢኮኖሚ ዘርፉ ውስጥ የሥራ ዕድሎችን ለማስፋፋት ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0