የናይጄሪያ መንግሥት ለወጣት የፈጠራ ባለሙያዎች የድጋፍ ፕሮግራም ጀመረ

ሰብስክራይብ

የናይጄሪያ መንግሥት ለወጣት የፈጠራ ባለሙያዎች የድጋፍ ፕሮግራም ጀመረ

በተማሪዎች የቬንቸር ካፒታል ድጋፍ ሥር ከፌዴራል መንግሥት ለእያንዳንዱ 45 ተማሪዎች የ36 ሺህ ዶላር ድጋፍ ማድረጉን የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

የናይጄሪያ የትምህርት ሚኒስትር ቱንጂ አላውሳ ለመገናኛ ብዙኃን እንደገለጹት፤ ፕሮግራሙ በዓለም ላይ የሚቀጥለውን የቴክኖሎጂ ማዕበል ሊመሩ የሚችሉ በፈጠራ ላይ ያተኮሩ ናይጄሪያውያን ተማሪዎችን በመላ ሀገሪቱ የመደገፍ ዓላማ አለው።

የተማሪዎች ቬንቸር ካፒታል ድጋፍ ለወጣት የፈጠራ ባለሙያዎች የሚከተሉትን ያቀርባል፡-

🟠 ያለምንም ድርሻ ክፍያ የሚሰጥ የገንዘብ ድጋፍ፣

🟠 የምክር አገልግሎት፣

🟠 የንግድ ማሳደጊያ ድጋፍ፣

🟠 የዲጂታል መሣሪያዎች።

"በፌዴራል የትምህርት ሚኒስቴር በኩል የሚተገበረው የተማሪዎች የቬንቸር ካፒታል ድጋፍ፤ ከግብርና እና ከጤና ጥበቃ ጀምሮ እስከ ሎጂስቲክስ እና ፊንቴክ ያሉ ሀገራዊ ችግሮችን የመፍታት አቅም ያላቸውን በተማሪዎች የሚመሩ አዳዲስ የንግድ ሥራዎችን ለመለየት፣ ለማሳደግ እና የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ የተነደፈ ነው" ሲሉ ቱንጂ አላውሳ መናገራቸውን የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ጠቅሰዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0