የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ደመወዛቸውን ለቆሰሉ ወታደሮች እና ለተሰዉ የጦር ኃይሎች ቤተሰቦች ለመስጠት ቃል ገቡ

ሰብስክራይብ

የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ደመወዛቸውን ለቆሰሉ ወታደሮች እና ለተሰዉ የጦር ኃይሎች ቤተሰቦች ለመስጠት ቃል ገቡ

ፕሬዝዳንት ቲኑቡ ለዚህ ተነሳሽነት ልዩ ሂሳብ እንዲከፈት ለዋና አካውንታንቱ መመሪያ የሰጡ ሲሆን ይህም እ.ኤ.አ በ2023 ሥልጣን ከያዙበት ጊዜ ጀምሮ ያለውን ደመወዛቸውን እንደሚያካትት ገልጸዋል።

ፈንዱ ካሉት የበጎ አድራጎት ፕሮግራሞች በተለየ መልኩ፤ በግዳጅ ላይ እያሉ የአካል ክፍሎች ማጣትን ጨምሮ ከባድ ጉዳቶች ለደረሰባቸው ወታደሮች የተለየ ድጋፍ ያደርጋል።

የጦር ሠራዊት አባላትን መርዳት "የቸርነት ተግባር ሳይሆን ግዴታ ነው" በማለት አጽንኦት የሰጡት ቲኑቡ፤ የክልል ገዥዎች፣ ብሔራዊ ምክር ቤቱ፣ የግሉ ዘርፍ እና የቅርብ አጋሮቻቸው አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0