የአፍሪካ ኅብረት በሶማሊያ መረጋጋት እንዲሰፍን እና ውይይት እንዲደረግ ጥሪ አቀረበ

የአፍሪካ ኅብረት
የአፍሪካ ኅብረት  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.03.2026
ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ኅብረት በሶማሊያ መረጋጋት እንዲሰፍን እና ውይይት እንዲደረግ ጥሪ አቀረበ

የኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀ መንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ባወጡት መግለጫ፣ የሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ግዛት እና ሁሉም "ባለድርሻ አካላት" ልዩነቶቻቸውን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ብሔራዊ የምክክር ምክር ቤቱን "በአግባቡ እንዲጠቀሙበት" አሳስበዋል።


"በፌዴራል መንግሥቱ እና በፌዴራል አባል ግዛቶች መካከል ያሉ ልዩነቶች በውይይት መፈታት አለባቸው" ሲል መግለጫው አመልክቷል።


የሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ግዛት፤ ታጣቂዎችን ያስታጥቃል እንዲሁም ቀጣናውን ያናጋል የሚል ክስ በማቅረብ ከፌዴራል መንግሥቱ ጋር ያለውን ትብብር መጋቢት 8 ቀን አቋርጧል። የፌዴራል መንግሥቱ በበኩሉ ውሳኔውን በማውገዝ ለውይይት ጥሪ አቅርቧል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0