ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የአፍሪካ የባሕል ስፖርቶች እና ጨዋታዎች ፌስቲቫልን እንድታዘጋጅ ተመረጠች
13:20 30.03.2026 (የተሻሻለ: 13:57 30.03.2026)

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የአፍሪካ የባሕል ስፖርቶች እና ጨዋታዎች ፌስቲቫልን እንድታዘጋጅ ተመረጠች
በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው የ2026 አኅጉራዊ ውድድር መላው አፍሪካውያን ልዩ ባሕላዊ ጨዋታዎቻቸውን ይዘው የሚቀርቡበት፣ የአኅጉሪቱ ወጣቶች የሚገናኙበት እና የባሕል ልውውጥ የሚያደርጉበት ደማቅ መድረክ ይሆናል ተብሏል።
የመጀመሪያው የአፍሪካ ባሕል ስፖርቶች ፌስቲቫል በኢትዮጵያ እንዲካሄድ መወሰኑ ለሀገራዊ ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ሲሉ የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ መኪዩ መሀመድ ተናግረዋል፡፡
የአፍሪካ ባሕል ስፖርቶች እና ጨዋታዎች ኮንፌዴሬሽን ሊቀመንበር ዶ/ር ኪይካማቱዋ፤ "ኢትዮጵያ የአፍሪካ ባሕል እና ታሪክ መገኛ በመሆኗ ይህንን ውድድር ለማዘጋጀት ተመርጣለች" ብለዋል።
በተያያዘም የአፍሪካ ባሕል ስፖርቶች እና ጨዋታዎች ኮንፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ ባሕል ስፖርቶች ፌዴሬሽን በቴክኒክ ድጋፍ፣ በሚዲያ አጠቃቀም፣ በባሕላዊ ጨዋታዎች ሕግጋት ዝግጅትና ሥልጠና ዙሪያ በጋራ ለመሥራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው የ2026 አኅጉራዊ ውድድር መላው አፍሪካውያን ልዩ ባሕላዊ ጨዋታዎቻቸውን ይዘው የሚቀርቡበት፣ የአኅጉሪቱ ወጣቶች የሚገናኙበት እና የባሕል ልውውጥ የሚያደርጉበት ደማቅ መድረክ ይሆናል ተብሏል።
የመጀመሪያው የአፍሪካ ባሕል ስፖርቶች ፌስቲቫል በኢትዮጵያ እንዲካሄድ መወሰኑ ለሀገራዊ ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ሲሉ የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ መኪዩ መሀመድ ተናግረዋል፡፡
የአፍሪካ ባሕል ስፖርቶች እና ጨዋታዎች ኮንፌዴሬሽን ሊቀመንበር ዶ/ር ኪይካማቱዋ፤ "ኢትዮጵያ የአፍሪካ ባሕል እና ታሪክ መገኛ በመሆኗ ይህንን ውድድር ለማዘጋጀት ተመርጣለች" ብለዋል።
በተያያዘም የአፍሪካ ባሕል ስፖርቶች እና ጨዋታዎች ኮንፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ ባሕል ስፖርቶች ፌዴሬሽን በቴክኒክ ድጋፍ፣ በሚዲያ አጠቃቀም፣ በባሕላዊ ጨዋታዎች ሕግጋት ዝግጅትና ሥልጠና ዙሪያ በጋራ ለመሥራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X