ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ለውጦች የደቡባዊ ዓለም ሀገራትን ሕብረት ይሻል - የበይነ ድርጅት ዋና ጸሐፊ
20:06 29.03.2026 (የተሻሻለ: 20:14 29.03.2026)
ሰብስክራይብ
ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ለውጦች የደቡባዊ ዓለም ሀገራትን ሕብረት ይሻል - የበይነ ድርጅት ዋና ጸሐፊ
በሦስት አኅጉራት የሚገኙ 79 ሀገራትን የሚያስተባብረው የአፍሪካ፣ የካሪቢያን እና የፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት፤ ጠንካራ እና ተደማጭነት ያለው ተቋም መሆን እንዳለበት ዋና ጸሐፊው ሙሳ ባትራኪ ተናግረዋል። ዋና ጸሐፊው ይህን ያሉት በኢኳቶሪያል ጊኒ ማላቦ በተካሄደው የድርጅቱ 50ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ጉባኤ ላይ ነው።
ድርጅቱ ወቅታዊ የጂኦፖለቲካዊ ተግዳሮቶችን ለመወጣት አራት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችን መከተል እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል፦
◾ የፖለቲካ ተገቢነት፦ በዋና ዋና ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ "የደቡባዊ ዓለም ሀገራትን አንድ ድምጽ" የሚያስተጋባ ስልታዊ መድረክ መሆን፣
◾ የተለያዩ አጋርነቶች፦ በደቡብ-ደቡብ እና በሦስትዮሽ የትብብር ማዕቀፎች አማካኝነት ግንኙነቶችን ዘመናዊ እና ተግባራዊ ማድረግ፣
◾ የሕዝብ እና የግል ዘርፍ ተሳትፎ፦ የሚጨበጥ ውጤት ለማምጣት ሴቶችን፣ ወጣቶችን እና የግል ዘርፉን የተግባር እንቅስቃሴዎች እምብርት ማድረግ፣
◾ የዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ፦ የኢንዱስትሪ አብዮትን ለመደገፍ እና ዘላቂ ልማትን ለማፋጠን ዘመናዊ መሣሪያዎችን ማቀናጀት።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X