የኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ልጅ 'ሀሰተኛ ፓስተሮች' እንዲታሰሩና የቲዎሎጂ ዲግሪ መስፈርት እንዲወጣ አሳሰቡ

ሰብስክራይብ

የኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ልጅ 'ሀሰተኛ ፓስተሮች' እንዲታሰሩና የቲዎሎጂ ዲግሪ መስፈርት እንዲወጣ አሳሰቡ

እ.ኤ.አ በ2024 የተመሰረተው 'የኡጋንዳ አርበኞች ሊግ' የሲቪክ ማኅበር እና የፖለቲካ ቡድን ስልጣን ከያዘ፤ የቤተ-ክርስቲያን መሪዎች የቲዎሎጂ ዲግሪ እንዲኖራቸው በማስገደድ ሕገ-ወጥ አሠራርን እንደሚዋጋ ሙሁዚ ኬይነሩጋባ ገልጸዋል።

የኡጋንዳ መከላከያ ኃይል አዛዥ እና የኡጋንዳ አርበኞች ሊግ ሊቀመንበር የሆኑት ሙሁዚ በኤክስ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ እንዲህ ያሉ ፓስተሮች "እግዚአብሔርን በማዋረድ" ወንጀል ይከሰሳሉ ብለዋል።

ይህ ሃሳብ ጎረቤት ሀገር ሩዋንዳ እ.ኤ.አ በ2018 ፓስተሮች የቲዎሎጂ ዲግሪ እንዲኖራቸው በማስገደድ የሐይማኖት አመራርን ሙያዊ ለማድረግ እና ምዕመናን ከብዝበዛ ለመከላከል ካደረገችው ማሻሻያ ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ መስፈርቱን ያላሟሉ በሺዎች የሚቆጠሩ አብያተ ክርስቲያናት መዘጋታቸው የሚታወስ ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0