የእስራኤል ጦር ለመጀመሪያ ጊዜ በሶሪያና ሊባኖስ አዋሳኝ ድንበር ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታወቀ
18:05 29.03.2026 (የተሻሻለ: 18:14 29.03.2026)
ሰብስክራይብ
የእስራኤል ጦር ለመጀመሪያ ጊዜ በሶሪያና ሊባኖስ አዋሳኝ ድንበር ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታወቀ
የእስራኤል መከላከያ ኃይል 810ኛ የተራራ ክፍለ ጦር፤ በሶሪያ ጎላን ኮረብታዎች ላይ ካለው ይዞታ በመነሳት ወደ ደቡብ ሊባኖስ ድንበር ተሻጋሪ ወታደራዊ ዘመቻ ማድረጉን የጦር ኃይሉ የፕሬስ አገልግሎት ዘግቧል።
በሶሪያ ግዛት ስር በሚገኘው በሄርሞን ተራራ በኩል ወደ ሸባ ፋርምስ አካባቢ የተካሄደው ይህ ዘመቻ፤ የሊባኖሱ ሄዝቦላህ በድንበር ቀጣናው እንዳይመሽግ ለመከላከልና የጸጥታ ስጋቶችን ለማስወገድ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ወረራው ከሄዝቦላህ ጋር ያለውን የውጊያ ሕግ ከመሠረቱ ሊቀይር እንደሚችልና የሶሪያን ጦር ጨምሮ በሁለቱም የድንበር አካባቢዎች የሚገኙ ኃይሎችን ወደ ሰፊ ግጭት የመግባታቸው ስጋት ከፍ እንዲል ማድረጉን የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
እርምጃው ዋሽንግተን የደማስቆ መንግሥት ሄዝቦላህን ለመመከት በሚደረገው ጥረት እንዲተባበር ጫና እያደረገች መሆኑ በሚነገርበት ወቅት የመጣ ነው።
ከእስራኤል መከላከያ ኃይል የተገኘ ተንቀሳቃሽ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X