የቀድሞው የአልጄሪያ ፕሬዚዳንት ሊያሚን ዘሩዋል በ84 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
18:09 29.03.2026 (የተሻሻለ: 18:15 29.03.2026)

ሰብስክራይብ
የቀድሞው የአልጄሪያ ፕሬዚዳንት ሊያሚን ዘሩዋል በ84 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
የቀድሞው መሪ በአልጀርስ በሚገኘው መሐመድ ሰጊር ነካሽ ወታደራዊ ሆስፒታል ለረጅም ጊዜ ህክምናቸውን ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ ማረፋቸው ተገልጿል። ይህን ተከትሎም በአልጄሪያ የሦስት ቀናት ብሔራዊ ሀዘን መታወጁን የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
🟠 ዘሩዋል እ.ኤ.አ ከ1994 እስከ 1999 የሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት ሆነው አገልግለዋል። ከዚያ በፊት ደግሞ ከ1993 እስከ 1994 የመከላከያ ሚኒስትር ነበሩ።
🟠 የነፃነት ትግል አርበኛ የነበሩት ዘሩዋል፤ የፈረንሳይን የቅኝ አገዛዝ ለመታገል ገና በ16 ዓመታቸው የብሔራዊ ነፃነት ጦርን ተቀላቅለዋል።
🟠 በኋላም በካይሮ፣ በሞስኮ እና በፓሪስ ወታደራዊ ሥልጠናዎችን ወስደዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
የቀድሞው መሪ በአልጀርስ በሚገኘው መሐመድ ሰጊር ነካሽ ወታደራዊ ሆስፒታል ለረጅም ጊዜ ህክምናቸውን ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ ማረፋቸው ተገልጿል። ይህን ተከትሎም በአልጄሪያ የሦስት ቀናት ብሔራዊ ሀዘን መታወጁን የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
🟠 ዘሩዋል እ.ኤ.አ ከ1994 እስከ 1999 የሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት ሆነው አገልግለዋል። ከዚያ በፊት ደግሞ ከ1993 እስከ 1994 የመከላከያ ሚኒስትር ነበሩ።
🟠 የነፃነት ትግል አርበኛ የነበሩት ዘሩዋል፤ የፈረንሳይን የቅኝ አገዛዝ ለመታገል ገና በ16 ዓመታቸው የብሔራዊ ነፃነት ጦርን ተቀላቅለዋል።
🟠 በኋላም በካይሮ፣ በሞስኮ እና በፓሪስ ወታደራዊ ሥልጠናዎችን ወስደዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X