የቀድሞው የአልጄሪያ ፕሬዚዳንት ሊያሚን ዘሩዋል በ84 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የቀድሞው የአልጄሪያ ፕሬዚዳንት
የቀድሞው የአልጄሪያ ፕሬዚዳንት - Sputnik አፍሪካ, 1920, 29.03.2026
ሰብስክራይብ
የቀድሞው የአልጄሪያ ፕሬዚዳንት ሊያሚን ዘሩዋል በ84 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የቀድሞው መሪ በአልጀርስ በሚገኘው መሐመድ ሰጊር ነካሽ ወታደራዊ ሆስፒታል ለረጅም ጊዜ ህክምናቸውን ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ ማረፋቸው ተገልጿል። ይህን ተከትሎም በአልጄሪያ የሦስት ቀናት ብሔራዊ ሀዘን መታወጁን የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

🟠 ዘሩዋል እ.ኤ.አ ከ1994 እስከ 1999 የሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት ሆነው አገልግለዋል። ከዚያ በፊት ደግሞ ከ1993 እስከ 1994 የመከላከያ ሚኒስትር ነበሩ።

🟠 የነፃነት ትግል አርበኛ የነበሩት ዘሩዋል፤ የፈረንሳይን የቅኝ አገዛዝ ለመታገል ገና በ16 ዓመታቸው የብሔራዊ ነፃነት ጦርን ተቀላቅለዋል።

🟠 በኋላም በካይሮ፣ በሞስኮ እና በፓሪስ ወታደራዊ ሥልጠናዎችን ወስደዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0