የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብን ከመፍረስ ለመታደግ የ100 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገ

የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ
የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 29.03.2026
ሰብስክራይብ
የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብን ከመፍረስ ለመታደግ የ100 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና ቢጂአይ ኢትዮጵያ በከፍተኛ የፋይናንስ ቀውስ ውስጥ የሚገኘውና ለወራት ተጫዋቾቹን ደሞዝ መክፈል ተስኖት ለነበረው አንጋፋው የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ የገንዘብ ድጋፉን አድርገዋል።

የክለቡን ወቅታዊ ሁኔታና መዋቅር ለማስተካከል ብሎም የአሠራር ሪፎርም ለማድረግ የተቋቋመው ጊዜያዊ ኮሚቴ ድጋፉን ለታለመለት ዓላማ የማዋል ኃላፊነት ተጥሎበታል።

ድጋፉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ በሆነው የፈረሰኞቹ ክለብ ላይ ተደቅኖ የነበረውን ስጋት ይቀርፋል ተብሎ የታመነበት ሲሆን በቀጣይ ክለቡን በዘላቂነት ወደ ቀድሞ ጥንካሬው ለመመለስ የሚያስችሉ የለውጥ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ተገልጿል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0